Latest News

በወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ ምክንያት ትምህርታቸውን አቋርጠው የነበሩ ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደረገላቸው

በወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ ለመማር ምቹ ባልሆኑ የጦርነት ቀጠና ውስጥ በነበሩ የተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች በትምህርት ገበታቸው ላይ የነበሩ እና ትምህርታቸው ለአንድ ዓመት ያህል አቋርጠው በትምህርት ሚኒስቴር ባደረገው ዳግም ምደባ ወደ ዩኒቨርስቲያችን ለመጡ ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደረገላቸው፡፡

በስነ ስርዓቱ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ዲን ዶ/ር ምኒችል ግታው ለተማሪዎቹ እንደተለፁት የቆያችሁበት ሁኔታ ፈተናው የናንተ ብቻ ሳይሆን የኛም፤ የሀገሪቱም ፈተና ነው ብለዋል፡፡ በዚህ ችግር ውስጥም ጥንካሬ እንማራለን፣ ለሌሎችም ማሰብን ትምህርት በመውሰድ መልካም ጎንኑ ለመመልከት በመሞከር ትምህርት መውሰድ ይቻላል ሲሉ ጠቁመዋል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትኩረት አድርጎ ከሚሰራባቸው አንዱ ተከባብሮ፣ ተዋዶ በመኖር ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ስክነት እና ብስለት ለሀገር እና ህዝብ አንድነት የሚኖራቸውን ጉልህ ሚና በእያንዳንዳችሁ ውስጥ እንዲኖር እንፈልጋለን ብለዋል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት አቶ ብርሃኑ ገድፍ በበኩላቸው በትምህርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ ተማሪዎች ዙሪያ የተሟላ መረጃ ስላልነበረ በዩኒቨርስቲያችን አንድ ሳምንትም ሆነ ከዛም በላይ ችግር ለገጠማቸው፤ ነባራዊውን ሁኔታ በመገንዘብ ላሳዩት ትዕግስት አመስግነዋል፡፡ ይህም ችግር ለቀጣይ እንዳይፈጠር ትምህርት ሚኒስቴር ወደፊት የሁሉንም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በመረጃ ቋት እንደሚያስቀምጥ ተስፋቸውን ገልፀዋል፡፡

አቶ ብርሃኑ አያይዘውም የተማሪ ዓላማ ተምሮ ለደረጃ መብቃት ነው፡፡ ስለዚህ ከዋና ዓላማችሁ ውጭ ስትሰማሩ እራስንም ሀገርንም ዋጋ የሚያስከፍል በመሆኑ ዓላማችሁን መሳት የለባችሁም፤ ዩኒቨርሲቲ ካወቃችሁበት ሰው የምትሆኑበት ካለወቃችሁበት ሰውነታችሁን የምታጡበት ነው ብለዋል፡፡

በዕለቱ የሬጅስትራርና አልሙናይ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት ዶ/ር ብርሌው እና የስነ-ልቦና ማማከር የስራ ክፍል ባልደረባ ዶ/ር አብዮት ለተማሪዎች መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

በመርሃ ግብሩም በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጅክ ኮሙኒኬሽን ም/ፕሬዝዳንት ስር የባህል ማዕከል የተለያዩ አስተማሪና አዝናኝ የሆኑ ጥዕመ ዜማዎችንና ግጥሞችን አቅርበዋል፡፡ 

 

በጦርነቱ ቆስለው ማገገሚያ ማዕከል ላሉ የሰራዊት አባላት የአልባሳት ድጋፍ ተደረገ

*********************************************************************

የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ መምህራን ‹‹አሁንም ያስፈልጋል›› በሚል መንፈስ ተነሳስተው በጦርነቱ ቆስለው በፈለገ-ሕይወት ሪፈራል ሆስፒታል ማገገሚያ ክፍል ለሚገኙ የመከላከያ ሰራዊት፣ልዩ ኃይል፣ፋኖ እና ሚሊሻ አባላት በ28/06/14 ዓ.ም የአልባሳት ድጋፍ አደረጉ፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ መምህር አቶ ነጋ እጅጉ፣ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መምህር አቶ ብሩክ ገድፍ እና የባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መምህር አቶ ይደግ ሙናና በጋራ በመተባበር 21‚970 (ሃያ አንድ ሺ ዘጠኝ መቶ ሰባ) ብር፤ ከሶሻል ሳይንስ ፋኩልቲና ከቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ማህበረሰብ ደግሞ 28‚000 (ሃያ ስምንት ሺ) ብር ከማርያም ኮንዶሚኒየም ነዋሪዎች መሰብሰባቸውን ተናግረዋል፡፡

ስለሆነም መምህራኖች በተሰበሰበው ብር እስካሁን ማገገሚያ ክፍል ያሉትን የሰራዊት አባላት ችግር በመገንዘብ 150 ቁምጣና ቲሸርት፤117 ሙሉ ቱታ በመግዛት በፈለገ-ሕይወት ሬፈራል ሆስፒታል ለሚገኙ በጦርነቱ ለተጎዱ የሰራዊት አባላት አበርክተዋል፡፡

አልባሳቱን የተረከቡት የሎጀስቲክስ አስተባባሪ ኮሬኔል ተሾመ ጌጡ ሲሆኑ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ጊዜያት በርካታ ድጋፎችን ያበረከተ ምስጉን ተቋም መሆኑን ገልፀው አልባሳቱ እዚህ ላሉት ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ ቦታዎች ሆነው ህክምናቸውን ለሚከታተሉ የቆሰሉ የሰራዊት አባላትም ሆኑ በጦርነቱ ለተጎዱ የማህበረሰብ ክፍሎች አስፈላጊነቱ እየታየ የቅድሚ ቅድሚያ የሚያስፈልጋቸውን በመለየትና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ለታለመለት ዓላማ እንደሚያውሉት አስገንዝበዋል፡፡

ዘጋቢ፡- ሙሉጎጃም አንዱዓለም

 

A delegation from the Regional English Language Office (RELO) of the U.S. Embassy was delighted to travel to Bahir Dar University to open a new English Access Microscholarship Program. Learn more: https://www.facebook.com/photo/?fbid=269313712026132&set=a.167504332207071

Geospatial Data & Technology Center (GDTC) of Bahir Dar University in collaboration with the Amhara National Regional State Environment, Forest & Wildlife Protection & Development Authority offer a GIS Training for Twenty-five Environmental & Social Impact Assessment and Environmental & Social Performance Auditing experts from the Zone, Woreda & Town Administration. The training was a hands-on training and held for seven days (February 25-March 03, 2022). 

Topics covered:

·            Basic concepts in GIS

·            Working with ArcGIS Environment

·            Geodatabase Design & Creation

·            Wrangling Data into Maps

·            Making Sense out of Spatial Data

·            How to use GPS?

·            Extract of features from Google Earth

  •  Application of GIS in Environmental & Social Impact Assessment and Performance  
  •   

 

 

English Access Microscholarship Program Kick Off held
===================================
The second English Access Microscholarship Program induction ceremony was held on March 05/2022 at Peda campus, Old Senate Hall, Bahir Dar University, Ethiopia.
In the opening event, Diane Millar, RELO - Representative of US Embassy, Addis Ababa expressed her excitement being in Bahir Dar noting that it is her first trip outside of Addis in her a year and half long stay in Ethiopia. Speaking on the launching of the second English Access Microscholarship program at Bahir Dar University, she expressed with regret that the program had been delayed due to COVID 19. In her speech, Diane thanked Bahir Dar University: Doctors: Tesfaye Shiferaw, V/president for Research and Community Services, Sefa Meka, Dean Faculty of Humanities and Dawit and Manendante, Access Coordinators for making this program a reality.
Diane said that English is beyond a language of instruction; it is a language of business and science, innovation and entrepreneurship. In the access program, she noted, students will learn not only about American culture but their own culture and values too, develop personally and grow into strong and confident leaders. She mentioned that this microscholarship is just the beginning, but there will be other undergrad and graduate program scholarship opportunities if students work hard and be competitive. She made students promise to work hard, respect their teachers and classmates, help their parents, enjoy and have fun in and through the program.
Finally, She thanked parents for their great parenting and for allowing their children work with the Access program and welcomed all to the international English Access Micro scholarship family.
Dr Sefa Meka, Dean Faculty of Humanities expressed his gratitude to the tax-paying American people and the American Embassy Addis Ababa for their financial aid to running the Access program that will help support the in demand highschool and preparatory students improve their English language competence and develop personally and intellectually. He congratulated the Access team at the faculty for winning the grant. He expressed his belief that the program will help benefit the local community students and wished all a successful undertaking.
Dr Yinager T/Sellassie spoke representing the office of the Vice President for Research and Community Services of BDU. He thanked the American Embassy for the continued support to improve the English Language teaching in Ethiopia. As an access teacher himself, he witnessed that the program was very successful in the first round and believed would still be better in current one.
In the event, Dr Manendante Mulugeta presented a project overview about the Access Micro scholarship program. He highlighted the major target areas of the program. The access package includes English language as its top priority, but the program also thrives to help students grow fully as individuals and hence engage them in community service and culture sharing activities. He gave a clear picture about the Access English Microsholarship Program.
In the ceremony, certificate handing over program to the Access participants was held. There was a getting to know each other program by Access teachers and there were also motivating language games which were powerful enough to hold the students attention. The event was co-chaired by Miss Mastewal Mesfin and Dr Dawit Amogne.
Message from the Access team: We are very grateful to the American People and the Embassy at Addis Ababa!
 
 

ለባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች በሙሉ

 

ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ አመት ትምህርታችሁን አጠናቃችሁ ዲፓርትመንት   ለመምረጥ በዝግጅት ላይየምትገኙ ተማሪዎች በሲኒማ እና ቴአትር ጥበባት መርሀ ግብር  (Cinema and Theatre Arts Program) ለመማር ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎች እስከ 29/06/2014 መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን፡-

መጋቢት 01/7/2014 ዓ.ም ጥዋት 3:00 ፔዳ ግቢ ኦዲትሪየም አዳራሽ የመግቢያ የሙከራ ፈተና ስለሚሰጥበተጠቀሰው ቀንና ቦታ በመገኘት መግቢያ ፈተናውን እንድትወስዱ እንገልፃለን፡፡  

መመዝገቢያ ቦታ:- ጆርናሊስም እና ስነ ተግባቦት ዲፓርትመንት ቢሮ እና በአካል መመዝገብ ለማትችሉ ከዚህ በታችበሚገኘዉ ሊንክ በኦንላይን (online) መመዝገብ እንደምትችሉ  እናሳስባለን:: 

ለመመዝገብ ሊንኩን ይጫኑ

https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSedN1H6dvcwVWX9Y0i6ivzSB2w7WjoH6b02MTp5f_poGsnoig/viewform?usp=sf_link

 

Bahir Dar University management met with representatives of the U.S. Embassy Addis Ababa

The management of Bahir Dar University discussed with members of the the Cultural Affairs Section, U.S. Embassy Addis Ababa about the longstanding bilateral partnerships between the two institutions and the commitments required from both sides to effectively run ongoing projects and intiatives. The discussion took place at the President Office of the University.

አድዋ ኢትዮጵያዊያንን ብቻ ሳይሆን መላውን ጥቁር ህዝቦች የነፃነት ድል ያጎናጸፈ ነው” ዶ/ር ፍሬዉ ተገኘ

የካቲት 23 ቀን 2014ዓ.ም (ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ)

የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬዉ ተገኘ እንደገለጹት የአድዋ ድል ሲነሳ የማንረሳቸዉ ሁለት ሰዎች አሉ፡- እነሱም እምዬ ሚኒሊክና እቴጌ ጣይቱን አለማንሳት አይቻልም ብለዋል፡፡ የዓለም ጥቁር ህዝቦች ለሚኒሊክ የሚሰጡትን ቦታ ያክል እኛ ኢትዮጵያውያን እየሰጠነዉ ስላልሆነ ይህ መታሰብ እንዳለበት ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል፡፡ አድዋ የኢትዮጵያውያንን ጀግንነትና ድል አድራጊነት በዓለም አደባባይ ከፍ ብሎ እንዲታወቅ ያደረገ የድል ታሪክ መሆኑንም ዶ/ር ፍሬዉ ገልጸዋል።

የአሁኑ ትውልድም አባቶቻችን ከጠላት ጋር ተናንቀው ነፃ ሀገር እንዳስረከቡን አውቆ ኢትዮጵያን በአንድነት ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ ማቆየት እንዳለበት አመልክተዋል። ዶ/ር ፍሬዉ አክለዉም የነፃነት ትግሉ አሁንም የሚቀጥል ነው፤አድዋን ዘክረነዉ ብቻ የሚያልፍ ሳይሆን ወደፊትም መልዕክት ይዘን የምንታገልበት ነው ብለዋል፡

የዩኒቨርሲቲው የታሪክ ምሁራንም በዓሉን የተመለከቱ ጥናታዊ ፅሁፎች ያቀረቡ ሲሆን ዶ/ር ገረመዉ እስከዚያ “የአድዋ ጦርነት” በሚል ርዕስ የጦርነቱን መነሻ ምክንያት፣ የጦርነቱን ደረጃዎችና በጦርነቱ የደረሱ ጉዳቶችን የቀደምት ታሪክ ጻህፍትን ስራዎች በማጣቀስ አቅርበዋል፡፡

ዶ/ር ገረመዉ የጦረነቱን መነሻ ሲያቀርቡ የአጤ ምኒልክ እና የኢጣሊያ ግንኙነት የተጀመረው ቀደም ባሉት ጊዜያት ቢሆንም በተለይ የአድዋ ጦርነት ፔትሮ አንቶኒሊ የሚባል ኢጣሊያዊ ከፈጠረዉ የዲፕሎማሲ ተንኮል ጋር ይያያዛል ብለዋል፡፡ በጦርነቱ የደረሱ ጉዳቶችም በርካታ እንደነበሩ ገልፀው በአድዋ ጦርነት 7,000 አካባቢ የጠላት ወታደሮች ሲገደሉ 1,428 ቆስለዋል፤ 3,000 የጦር ምርኮኛ ሆነዋል፡፡ በአንፃሩ በኢትዮጵያ በኩል ከ4,000—6,000 የሚደርሱ ተዋጊዎች በጀግንነት ሲሰው 8,000 ደግሞ መቁሰላቸውን ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሁፍ አብራርተዋል፡፡

ሌላው የፅሁፍ አቅራቢ አቶ ሰሎሞን አሻግሬ በበኩላቸዉ “ከአድዋ የምንወስዳቸው ትምህርቶች” በሚል ርዕስ በጦርነቱ ወቅት የነበረውን ጀግንነት፣ርህራሄ፣ህዝባዊ ተሳትፎ፣ጥንቃቄ እና ሀገራዊ የፖለቲካ አንድነት በማንሳት ለተሳታፊዎች በወቅቱ የነበረዉን ሁኔታ አስገንዝበዋል፡፡ ተሳታፊዎችም በቀረቡት ፅሁፎች ላይ ሰፋ ያለ ጥያቄና አስተያየት ያቀረቡ ሲሆን ከመድረኩ ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

በበዓሉ መነባንብ፣ ግጥም፣ አጭር ተውኔት እና በአማራ ፖሊስ ማርች ባንድ የቀረቡ ጥዑመ  ዜማዎች ለበዓሉ ድምቀት ከፍተኛ ሚና ነበራቸው፡፡

 126ኛው የአድዋ ድል በዓል የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንትና ከፍተኛ አመራሮች፣ የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች፣ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች እና የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች በተገኙበት የካቲት 23/2014 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲዉ ጥበብ ህንጻ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተከብሯል፡፡

   

ዘጋቢ፦ ሸጋዉ መስፍን

 
 
 
 
 
ReplyForward
 
 
 
 
 
 
 
 
 
 
 
 
 
 

በሀገራዊ የምክክር ሂደት እና አስፈላጊነት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ተካሄደ

*****************************************************************

የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ ልታካሂደው ላቀደችው አገራዊ ምክክር መድረክ ግንዛቤ የፈጠረ ምሁራዊ የምክክር ጉባኤ "በሐገራዊ  ምክክር  ሂደት  የባለድርሻ አካላት  ሚናና  ኃላፊነት" በሚል መሪ ቃል የካቲት 22/2014 ዓ.ም በጥበብ ህንጻ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የመንግስትና የግል የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲሁም መምህራንና ተማሪዎች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡

 የምክክር መድረኩን በንግግር የከፈቱት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ  አሁን ላይ ኢትዮጵያ ካለችበት ነባራዊ ሁኔታ አንፃር የእኛ እና የነሱ ፖለቲካ  ውሉ የጠፋበት ድሮ የማናውቀው ህይወት የሚከፈልበት፣ሕዝብ የሚሰቃይበት እና የሀገር ሀብት የሚወድምበት  እንደሀገር ችግር ውስጥ የገባንበት እንቆቅልሽ ውስጥ ስለሆንን ችግሩን ለመፍታት ዕውቀት ፣ጥበብና በጥልቀት ማሰብን እንደሚጠይቅ ተናግረው አገራዊ ምክክር መድረክ እንዲሳካ ከምሁራን ብዙ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል፡፡

በምሁራዊ የምክክር ጉባኤ ላይ በቅርቡ የተቋቋመውን አገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስመልክቶ ሦስት ጥናታዊ ወረቀቶች ቀርበዋል፡፡ የሰላም እና የግጭት ተንታኝ፣ የግጭት አፈታት ባለሙያ፣ በማንነት ላይ የተመሰረተ የግጭት ተመራማሪ፣ አቶ ድጋፌ ደባልቄ “ Large Group identity: Moving in and out of “ Glory” and Trauma” በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ፋኩልቲ መምህር፣ ዶ/ር አደም ካሴ “ብሔራዊ ውይይት ለምን፣ ለማን እና እንዴት፡ አንፃራዊ እሳቤዎችና ግንዛቤዎች”  የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የህግ መምህር የሆኑት ረዳት ፕ/ር ወርቁ ያዜ “በሀገራዊ የፖለቲካ ምክክር ሂደት የአማራ ተሳትፎ፡- የአማራ የፖለቲካ ኃይሎች ሚና እና ኃላፊነት” በሚሉ ርዕሶች የመወያያ ጥናታዊ ወረቀቶች ቀርበዋል፡፡

የውይይቱ ተሳታፊዎች በቀረቡት ጥናታዊ ወረቀቶችን ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችን እና አስተያየቶችን በማንሳት ሰፋ ያለ ውይይት ተካሂዷል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር እሰይ ከበደ ሀገራችን ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ሁኔታ ስናይ  የውስጥን ችግር  ምክንያት በማድረግ ምዕራባዊያን  ሀገራት ለራሳቸው የፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ የተለያዩ ደባዎችን እየሰሩ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ እኛ ኢትዮጵያዊያን የጠላቶቻችን አካሄድና ሁኔታ በመገንዘብ እንደ ሀገር ሕዝባዊ አንድነትን በማጠናከር ሀገራችንን ከመፍረስ ልንታደጋት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በማንነቱ የተነሳ መፈናቀልን፣ መገደልን፣ መሳደድን በተደጋጋሚ እያስተናገደ በስጋት እንዲኖር የተደረገው የአማራ ህዝብን የማያግባባ የህገ-መንግስቱ ጉዳይ ብዙ ማሻሻያ እንደሚያስፈልግ እና የሀገራዊ ምክክሩ ቢዘገይም ሀገር ነውና መደረጉ ተገቢ መሆኑን ዶ/ር እሰይ ተናግረዋል፡፡

በውይይቱ ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት፣ የዩኒቨርሲቲው መምህራን እና  ማሕበረሰብ  እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው የ2ኛ ዲግሪና 3ኛ ዲግሪ ተማሪዎች ተሳትፈውበታል፡፡

Pages