Latest News

All Interested are cordially invited!

Geospatial Data & Technology Center (GDTC) of Bahir Dar University in partnership with the Geographic Information Systems Society of Ethiopia offers a three-day hands-on GEE training August 15-17, 2022) for its staff.

This training which runs from August 15 – 17 , 2022 covers the GEE Code Editor, hands-on exercises on change detection, time series analysis, NDVI calculation, land use/ Land cover classification, and accuracy assessment of optical imagery. 

Google Earth Engine (GEE) for resource management is becoming one of the most essential tools in the scientific and decision-making community. GEE provides unparalleled access to large-scale data analysis through cloud computing technology without the need for any locally stored data or software.

 

Dr. Solomon Abedom ( from NTNU), a former student of Gash Ademe Mekonnen, has shared us his memory of a day he and his classmates owe their Mathematics instructor, the iconic Gash Ademe Mekonnen, a debt of gratitude.
Ademe Mekonnen (Associate Professor at AAU) a.k.a “ Galileo” was among the best instructors in the Department of Mathematics at Peda. He has published a book entitled: "Logic and Set Theory".
Read the attached file for the full account of the story by a former student of BDU.
Thank you Dr. Solomon Abedom!
Dr. Solomon Abedom ( from NTNU), a former student of Gash Ademe Mekonnen, has shared us his memory of a day he and his classmates owe their Mathematics instructor, the iconic Gash Ademe Mekonnen, a debt of gratitude.
Ademe Mekonnen (Associate Professor at AAU) a.k.a “ Galileo” was among the best instructors in the Department of Mathematics at Peda. He has published a book entitled: "Logic and Set Theory".
Read the attached file for the full account of the story by a former student of BDU.
Thank you Dr. Solomon Abedom!

ቀን፡-04/12/2014ዓ.ም

ማስታወቂያ

ለ ባሕር ዳር ከተማ የታዳጊ እግር ኳስ ፕሮጀክት ማሰልጠኛ ጣቢያዎች

ባህር ዳር

ጉዳዩ፡- የውድድር ተሳትፎ ጥሪ ስለማድረግ፤

 

እነሆ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ሁለተኛው ዙር የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የታዳጊ እግር ኳስ ፕሮጀክት ማሰልጠኛ ጣቢያዎች ውድድር ሊጀመር ነው፡፡ ሁለተኛው አመት የታዳጊ ወጣቶች  ውድድር ከ 16 አመት በታች የወንድና ከ 17 አመት  በታች የሴት ውድድር ብቻ ያካተተ ሲሆን በእነዚህ የእድሜ እርከን የምታሰለጥኑ የስልጠና ጣቢያ አሰልጣኞች ከ 5/12/2014 ዓ/ም እስከ 7/12/2014 ዓ/ም ድረስ ብቻ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ቢሮ ቁጥር 1 በመምጣት እንድትመዘገቡ ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡

ማሳሰቢያ

1. አንድ ማሰልጠኛ ጣቢያ 1 ቡድን ብቻ ያሳትፋል፤

2.  የእድሜ ምርመራ ማለፍ ይጠበቅባችዋል ፤

3.  ሁሉም ቡድኖች በማሰልጠኛ ጣቢያ ወይም በ ፕሮጀክት ተይዘው እየሰሩ መሆኑን ማረጋገጫ ማቅረብ  አለባችው፡፡

ለውሃ አካሚ ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ

(ሀምሌ 28/2014ዓ.ም፣ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-BDU) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ከዩኒቨርሲቲው ስልጠና ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር ከ30 በላይ ለሚሆኑ የውሃ አካሚ ባለሙያዎች ለ3 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ በተግባር ላይ የተመሰረተ ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ሙላቱ ጠብቀው እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው ካሁን በፊት ንፁህ የመጠጥ ውሃ ያገኝ የነበረው ከባሕር ዳር ከተማ ውሃ አገልግሎት ነበር፡፡ ከአንድ አመት በፊት የዩኒቨርሲቲውን የስነ-ምድር ት/ቤት መምህራን ጥናት መሰረት በማድረግ ሰባታሚት አካባቢ ከ127 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ አድርጎ ያስገነባውን ውሃ አክሞ ለተጠቃሚው የዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ጥቅም እንዲውል የሚያስችል የባለሙያዎች ስልጠና እንደሆነ ተገልጿል፡፡

ኃላፊው አክለውም ስልጠናው ከሁሉም ግቢዎች ለተውጣጡ ከ30 በላይ ለሚሆኑ የውሃ አካሚ ባለሙያዎች በተግባር ላይ ተመስርቶ ለ3 ተከታታይ ቀናት ይሰጣል፡፡ ሠልጣኞችም በሰለጠኑበት ሙያ መሰረታዊ ዕውቀት ይዘው ወደ ስራ እንደሚገቡ ይጠበቃል ብለዋል፡፡

ስልጠናውን የሰጡት የባሕር ዳር ከተማ ውሃ አገልግሎት ከፍተኛ የጥራት ባለሙያ አቶ ኃይለእየሱስ ጓዴ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ብዙ ቁጥር ያለው ማህበረሰብን አቅፎ እንደመያዙ እና የራሱን ውሃ ማስተዳደር በመጀመሩ የውሃ አቅርቦቱ ጥራቱን የጠበቀ ይሆን ዘንድ ሙያዊ ድጋፍ ለማድረግ ስልጠናውን ሊሰጡ እንደቻሉ ተናግረዋል፡፡ የሚሰጡትም ስልጠናዎች የውሃ ጥራትን መለካት እና ውሃውን ከብክለት ለመከላከል የሚያስችል ሲሆን ባለድርሻ አካላትም ሆነ ኃላፊዎች ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ አሳስበዋል፡፡ የስልጠናውም ዓላማ ብቁ እና ጤናማ የሆነ ማህበረሰብ በዩኒቨርሲቲው ላይ መገንባት ነው፡፡      

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU

Description: 💦Description: 💦Description: 💦Description: 💧Description: 💦Description: 💦Description: 💧Description: 💦Description: 💦Description: 💦

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎

Thank you for Inviting, like, share & visiting BDU page!

ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:- https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

#BDU60th_ANNIVERSARY

 

የኢትዮጵያ ጨርቃጨርቅና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (EiTEX) እና ምህረት ሜዲካል አቅርቦት ግሩፕ በጋራ ለመስራት ተስማሙ

Foe the details click on : https://www.facebook.com/eitex.et/posts/pfbid0oB3UrTFaB6KT8b2eLqo4YRCAwP...

BDU’s alumni, current presidents of local universities

Former graduates of Peda and Poly of the current Bahir Dar University currently serving as presidents of Debre-Markos (Dr.Tafere), Ambo (Dr. Beyissa), Arbaminch (Dr. Damtew), Kotebe Education (Dr. Berhanemeskel), Assosa (Dr. Kemal), Debre-Tabor (Dr. Anegageregn), Adama (Dr. Lemmi), Gondar (Dr. Asrat), Worabe (Dr. Tofiq) and Wollo (Dr. Mengesha) universities having a group photo together with BDU's president Dr. Firew Tegegne along the shore of lake Tana and Peda's auditorium.

3ኛው የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ተካሄደ
 
(ሀምሌ 24 /2014ዓ.ም፣ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-BDU) የፌደራል ግዥና ንብረት ባለስልጣን ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ከመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች እና ከባለደርሻ አካላት ጋር በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበብ አዳራሽ ውይይት ተካሄደ፡፡
 
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ ዩኒቨርሲቲው እየሰራቸው ያሉትን ዋና ዋና ተግባራት ለተወያዮቹ ገለጻ አድርገዋል፡፡ ግቢዎችን ውብና ማራኪ የማድረግ ሥራ እየተሰራ መሆኑን፣ ለባሕር ዳር ከተማ እና ለአካባቢው ማህበረሰብ ችግር ፈቺ የሆነ ጥናትና ምርምር እያደረገ እንደሆነ፣ ዩኒቨርሲቲው ግንባር ቀደም የምርምር ዩኒቨርሲቲ እና የልህቀት ማዕከል ለመሆን በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም እያንዳንዱ ግቢ በውስጡ የሚያከናውናቸውን አንኳር አንኳር ስራዎች አብራርተዋል፡፡
 
የመንግስት ግዥ እና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሃጂ ኢብሳ በበኩላቸው በዚህ የምክክር መድረክ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶችንና ም/ፕሬዚዳንቶችን መሰብሰብ ያስፈለገበት ምክንያት ግዥ የኃላፊዎች ሥራ በመሆኑና ያለውን ትንሽ ገንዘብ ቆጥቦ ውጤታማ በሆነ ነገር ላይ እንዲውል የማድረግ ኃላፊነት እንዳለባችሁ ለማስገንዘብ ነው ብለዋል፡፡ አቶ ሀጂ ኢብሳ አክለውም በዚህ ዓመት ከተመደበው በጀት 65 በመቶ የሚሆነው የሚውለው ለግዥ አገልግሎት ሲሆን ከዚህ ውስጥ በሀገር ደረጃ ከሚመደብ በጀት ትልቁን ድርሻ የሚወስዱት ዩኒቨርሲቲዎች እና ትምህርት ሚኒሲቴር ነው ብለዋል፡፡
 
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ አደም ፋራህ ከዚህ የምክክር መድረክ የሚገኙ ግብዓቶችን እንደ ዩኒቨርሲቲ መጠቀምና እንደ ሀገርም ለሌሎች ተቋማት የሚጠቅሙ ሀሳቦችን ይዞ በቀጣይ ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ለዚህ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን ከምክክር መድረኩ የሚገኙ ግብዓቶችን በአግባቡ በማደራጀት በቀጣይ እንደሀገር በግዥ ዙሪያ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት እና የግዥ ስርዓቱን ለማዘመን ለሚመለከተው አካል እንዲያቀርብ አሳስበዋል፡፡
 
“የመንግስት ግዥ አፈጻጸም ከልዩ ፈቃድና የተማሪዎች ምግብ አንጻር የሚታዩ ተግዳሮቶች ”በሚል ርዕስ በአቶ ገብያው ይታይህ የመንግስት ግዥ እና ንብረት ባለስልጣን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር፣ “በመንግስት ግዥ የአቤቱታና ጥፋተኝነት አፈጻጻም” በአቶ ደምሱ አብዲ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የአቤቱታ እና ጥፋተኝነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር፣ “የህጋዊነት ኦዲት አፈጻጸም የሚስተዋሉ ተግዳሮቶች በተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች” በአቶ አዲስ ጎዳና የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የኦዲት እና ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር፣ “ግዥ ለአካባቢ እና ለዘላቂ ልማት” በዶ/ር ማቴዎስ እንሰርሙ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደርና ልማት ም/ፕሬዚዳንት፣ “በከፍተኛ ትምህርት የግንባታ ግዥና ውል አስተዳደር የሚስተዋሉ ችግሮች” በዶ/ር ተመስገን ወንድሙ ከአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ “በዩኒቨርሲቲ የፕሮጀክት አስተዳደር ተግዳሮቶች” በአቶ ማተቤ ከኮንስትራክሽን ሥራዎች ተቆጣጣሪ ባለስልጣን እና “ዘመናዊ የንብረት አስተዳደርና የነዳጅ አጠቃቀም” በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተሰኙ ጽሑፎች ለውይይት ቀርበዋል፡፡
 
በመድረኩ ላይ ተገኝተው ማጠቃለያ የሰጡት የኤፌዴሪ ትምህርት ሚኒሲቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ለግዥም ሆነ ለፋይናንስ ህግ ያስፈልገናል ሲሉ፤ የህጉ ዓላማ ግን ተቋምን ለማሰር መሆን የለበትም፤ ይልቁንም ተቋም ሰርቶ፣ ተልዕኮ አሳክቶ ሀገር የሚቀይር የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ መሆን አለበት ብለዋል፡፡ አክለውም ኦዲትን በተመለከተ የክዋኔም፣ የግዥም፣ የፋይናንስም ኦዲት ሲደረጉ የሀገር መገለጫ ይሆናል፣ የተቋማት መሻሻል የሀገር መሻሻል ነው፡፡ ኦዲቶች ከመሰረተ ሀሳብ ጋር መያያዝ አለበት ፎርሙን ብቻ ተከትለን መሆን የለበትም ብለዋል፡፡
 
በመጨረሻም በዩኒቨርሲቲው ያሉ የተለያዩ ግቢዎች የምድረ-ግቢ እና የአረንጓዴ ልማት ስራዎች የተጎበኙ ሲሆን ጎብኝዎችም በጉብኝታቸው ጽዱ፣ ውብና ማራኪ ስራዎች በዩኒቨርሲቲው መሰራታቸውን በማየታቸው መደሰታቸውንና ወደየ ዩኒቨርሲቲአቸው ሲሄዱ የወሰዱትን ልምድና ተሞክሮ ለመተግበር ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU
ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ
Wisdom at the source of Blue Nile
Thank you for visiting our
የተማሪዎች ፈጠራ ስራ ለዕይ ታቀረበ
*******************************
(ሀምሌ 24/2014 ዓ.ም፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-BDU) የባሕር ዳር ሳይንስ ኢንኩቤሽን ማዕከል/STEM/ ተማሪዎች በscience project, Calculator for blind people, ICT projects, Electronics and Rebottles, Preventing drunk driving, payroll formulation ላይ የሠሯቸው የፈጠራ ስራዎች የተማሪ ወላጆች እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ለዕይታ ቀረቡ፡፡
 
በስነ-ስርዓቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳት ዶ/ር ተስፋዬ ሽፈራው ወላጆች የልጆቻቸውን የፈጠራ ውጤት እንዲያዩ እና ለቀጣይ እንዲያበረታቷቸው ሌሎች ደግሞ ይህን በማየት እንዲነሳሱ ታስቦ መዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡
ዶ/ር ተስፋዬ አክለውም በዚህ ማዕከል የሚማሩ ተማሪዎች ከመደበኛ ትምህርት ቤቶች ከሚማሩ ተማሪዎች በተሻለ መልኩ እንዲሰሩ፣ ፈጠራ እንዲፈጥሩ ታስቦ ሲሆን ተማሪዎች በማዕከሉ ፕሮጀክት የማይሰሩ ከሆነ መቀጠል እንደማይችሉ ተናግረዋል፡፡
የባሕር ዳር ሳይንስ ኢንኩቤሽን ማዕከል ዳይሬክተር ዶ/ር ተስፋ ተገኘ በበኩላቸው በማዕከሉ ስድስት ፕሮግራሞች መኖራቸውን ሲጠቅሱ ከ9ኛ ክፍል ጀምሮ ባሕር ዳር ከሚገኙ የተለያዩ ት/ቤቶች በየዓመቱ 50 ተማሪዎችን ተቀብሎ ያስተምራል እንዲሁም ከ5ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ሳይንስን በተግባር ለ45 ቀናት ስልጠና ይሰጣል፡፡
ባሕር ዳር እና በአካባቢው የሚገኙ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች አምስት አምስት ሴት ተማሪዎች ተመርጠው በዩኒቨርሲቲው ለ9 ቀናት በሰሚስተር በሚኖረው እረፍት ሳይንስን በተግባር እየተማሩ ከሌሎች ጋር አብሮ የመኖርን ልምድ ይቀስማሉ፣ ማዕከሉ በአገር አቀፍ ደረጃ በሚደረገው የፈጠራ ስራ ውድድር እንዲሳተፉ ድጋፍ ያደረጋል፣ የህፃናት ፕሮግራም ከ4ኛ እስከ 6ኛ ለሚማሩ ተማሪዎች በቅዳሜ እና እሁድ ቀናቶች ያሰለጥናል፣ባሕር ዳር እና አካባቢው የሚገኙ ተማሪዎች ቤተ ሙከራውን መጠቀም ሲፈልጉ ቀድመው ያሳውቁና ማዕከሉ ውስጥ እንዲሰሩይደረጋል ብለዋል ዶ/ር ተስፋ፡፡
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU
ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ
Wisdom at the source of Blue Nile
Thank you for visiting our page!
ለተጨማሪመረጃዎች፡-
Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official
website :- www.bdu.edu.et
#BDU60th_ANNIVERSARY

Pages