Latest News

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በቤዛዊት ተራራ ላይ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም አካሄደ

(ሐምሌ 04/2014 ዓ.ም፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-BDU) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ቢሮ የዩኒቨርሲቲውን መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች በማስተባበር ከሶሳይቲ ፎር ኢኮቱሪዝም ኤንድ ባዮዳይቨርሲቲ ኮንሰርቬሽን በጎ አድራጎት ማኅበር ጋር በመተባበር ቤዛዊት ተራራ ላይ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄዱ፡፡

በችግኝ ተከላው ላይ ተግኝተው ሲያስተባብሩ ያገኘናቸው የሶሳይቲ ፎር ኢኮቱሪዝም ኤንድ ባዮዳይቨርሲቲ ኮንሰርቬሽን ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ  ትዝታ የኔዓለም ማኅበሩ ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በየዓመቱ የችግኝ ተካላ እንደሚያካሂድ ተናግረው በእለቱ ከዩኒቨርሲቲው ጋር  በመሆን  በቤዛዊት ተራራ  ላይ ተንሰራፍቶ የነበረውን መጤ አረም (ላንታና ካማራን) በማፅዳት በማሕበሩ የችግኝ ጣቢያዎች የለሙ ሐገር በቀል ዛፎችን  መትከላቸውን ተናግረዋል፡፡

ስራ አስኪያጇ አክለውም ተራራውን በአገር በቀል ችግኝ ለማልማት በርካታ ችግኞች በችግኝ ጣቢያቸው እንዳሉና ቀደም ሲል  በመጤ አረም (ላንታና) የተወረረውን የተራራውን ክፍል የማፅዳት ስራ መሰራቱን ተናግረዋል፡፡ ሆኖም ግን መጤ አረሙን ለማስወገድ በየጊዜው ክትትል የሚፈልግ ስራ በመሆኑ ወጥና ቀጣይነት ያለው የተፈጥሮ ሐብት ስራን ለመስራት እና በየዓመቱ የሚተከሉ ችግኞች ከሰው እና ከእንስሳት ንክኪ ነፃ በማድረግ እና ውሃ በማጠጣት፤ በመኮትኮት ችግኞችን የሚንከባከቡ በርካታ የሰው ሃይል በመቅጠር ዘላቂነት ያለው የተፈጥሮ ሐብት ስራ እየተሰራ  መሆኑን ስራ አስኪያጇ ተናግረዋል፡፡

የችግኝ ተከላው ፕሮግራም አስተባባሪና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ተቀዳሚ ዳይሬክተር ዶ/ር ተሰማ አይናለም  በበኩላቸው  የችግኝ ተከላ ፕሮግራሙ ዩኒቨርሲቲው እንደሃገር የአረንጓዴ አሻራ (Green legacy) ተብሎ ከመነገሩ በፊት ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ በይልማና ዴንሳ፣ ቋሪት እና ሰከላ ወረዳዎች  አዋሳኝ በሆነው ብር አዳማ አካባቢ እና በመራይ  እንዲሁም በቤዛዊት ተራራ ላይ እየተሰራ ያለ የተፈጥሮ ሐብት ስራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዳይሬክተሩ አክለውም በ2014 ዓ.ም ዓመቱን ሙሉ ሲለሙ የቆዩ የተለያዩ ሀገር በቀል ችግኞችን በቅርቡ የብር ዓዳማ ተራራን ጨምሮ በሌሎች ቦታዎችን ላይ የመትከል መርሃ ግብር እንደሚካሄድ አክለው ተናግረዋል፡፡ የቤዛዊት ተራራ  አካባቢው ድንጋያማ በመሆኑ ለአካባቢው ተስማሚ የሆኑ የግራቢያ ችግኞችን ከሶሳይቲ ኢኮ-ቱሪዝም ከተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ችግኞች እንደተተከሉ ገልፀዋል፡፡

በችግኝ ተካላ መርሃ ግብሩ ላይ ከሁሉም ግቢዎች የተወጣጡ መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች ተሳትፈዋል፡፡

 

 

STEM Center-BDU offers entrance examination  at Jan-MosKov Library to recruit new grade 9 entrants for the 2015 E.C. academic year.

STEM Center at Bahir Dar University has been accepting students who have just been promoted to grade 9 and have a love for science to train them until they finish their high school studies for a few years now. For the program, students have been recruited on merit basis. In relation to this, nearly 150 students sit for the entrance examination today. The exam included a collection of questions from five subjects namely Maths, Physics, Chemistry, Biology and English.  It is learnt that nearly one third of the students will be accepted for the new academic year.  

Among other things the center has been conducting the summer outreach program which aims to provide hands-on training to upper elementary and high school students from Bahir Dar. This program and other similar hands-on training schemes delivered by highly qualified University professors from BDU aim at sparking interest in science for those students who barely get the chance to see scientific experiments in their schools.

We would like to warmly welcome our new students at STEM-BDU!

An article about “Collaborative Monitoring for Sustainable Development of Lake Tana UNESCO Biosphere Reserve (CoMon)” project was published in an Austrian newspaper “Die Presse - a national Austrian daily newspaper published in Vienna.
The CoMon project is a joint project of the Carinthia University of Applied Sciences, Austria, and the Geospatial Data & Technology Center of Bahir Dar University.
The article is published in German, but beneath can be the title and the central theme of the article in English.
 
LAKE TANA፡ ‘’Where immigrated plants threaten nature and fisheries’’ In his article, it is intended to explore how the large biosphere reserve on Lake Tana can be optimally managed and how invasive species can be documented.
"Leadership Role In Quality Culture"
በሚል ርዕስ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ጥራት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት "Leadership Role in Quality Culture" በሚል ርዕስ ዙሪያ ከሁሉም ግቢ ለተውጣጡ የዩኒቨርሲቲው አመራሮችና መምህራን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ በሆኑት በፕሮፌሰር ዳንኤል ቅጣው በጥበብ ሕንፃ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በ01/11/14 ዓ.ም ስልጠና ተሰጠ፡፡
 
ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ ለአሰልጣኙና ለመላው ታዳሚ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው ጥራት የዩኒቨርሲቲው መገለጫ ከሆኑት ዋና ዋና እሴቶች አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
 
ፕሬዘዳንቱ በማስከተል ከሌሎች ልቆ ለመገኘት በእውቀት ላይ የተመሰረተ የአሰራር ስርዓት መዘርጋት እና በሀገራችን ብሎም ከዓለም ሀገራት ጋር ተወዳዳሪ ለመሆን ተቋማችን በማሪታይም አካዳሚ፣ በባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፣በኢትዮጲያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ እንዲሁም በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የተሰሩ ስራዎች እና የተሰጣቸው እውቅና ዩኒቨርሲቲውን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንደሚያደርገው አስገንዝበዋል፡፡
 
ዶ/ር ፍሬው አክለውም ዩኒቨርሲቲው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከ72 በላይ ስማርት ቦርድ በማስመጣትና በርካታ ስማርት የመማሪያ ክፍሎች በማዘጋጀት፣አዳዲስ ህንፃዎችን በማስገንባት፣በሁሉም ግቢዎች የተሰሩት የምድረ ውበት ስራዎች የጥራት መገለጫዎች እንደሆኑና ለሌሎች ተቋማት በሞዴልነት የሚታዩ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪም በመማር ማስተማሩም ሆነ በምርምሩ ከወትሮው በተለዬ መልኩ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት ጥራትን መሰረት አድርጎ መስራት አስፈላጊ በመሆኑ ቀሪ ክፍተቶችን ለመሙላት ስልጠናው ጉልህ ፋይዳ ስላለው ሁሉም የተቋሙ መምህራን ትኩረት ሰጥቶ እንዲከታተልና በተግባር ላይ እንዲያውለው ፕሬዘዳንቱ አሳስበዋል፡፡
 
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ጥራት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር አንዳርጋቸው ሞገስ በበኩላቸው የስልጠናው ዓላማ በዩኒቨርሲቲው በርካታ አኩሪ ተግባራት እየተከናወኑ ስለሆነ ሁሉም ስራ በጥራት የተደገፈ ለማድረግ ታልሞ በዩኒቨርሲቲው በሁሉም ግቢዎች ያሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ዲኖች፣ም/ዲኖችና ከኮርስ ቸሮችን ጨምሮ እስከ ትምህርት ክፍል ተጠሪ ድረስ ላሉ የስራ ኃላፊዎች እንደተሰጠ አውስተዋል፡፡ አክለውም ሰልጣኞች ያገኙትን ክህሎት ለሌሎችም በማካፈል ተደራሽነቱ እንዲሰፋ በማሰብ ስልጠናው መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡
እንደ ዳይሬክተሩ ጥራት ከሌሎች ከፍ ብሎ ለመገኘት አንኳር ጉዳይ ስለሆነ አሰልጣኙ በሙያው የካበተ ልምድ ስላላቸው ሰልጣኞች በርካታ ክህሎት እንደሚያገኙና ለወደፊት ሁሉም የስራ ኃላፊ በእቅድ ውስጥ በማስገባት ጥራትን መሰረት ያደረገ ስራ በዩኒቨርሲቲው እንዲሰፍን አሳስበዋል፡፡
 
አሰልጣኙ በውጭም ሆነ በአገር ውስጥ ስለጥራት ምንነትና አስፈላጊነት የካበተ ልምድ ያላቸው እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ዳንኤል ቅጣው ጥራት የውጭም ሆነ የውስጥ ደንበኛን ለማርካት ፋይዳው የጎላ ስለሆነ በጥራት ቀድሞ መገኘት ተገቢ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
 
ፕሮፌሰሩ በማስከተል በጥራት ዙሪያ ያለው ውድድር የርዕስ በርዕስ ሳይሆን ዓለም አቀፍ መሆኑን አስገንዝበው ዩኒቨርሲቲው ጥራት ያለው ተማሪ ለማፍራት ጥራት ያለው መምህር ሊኖረው እንደሚገባ በአንክሮ ተናግረዋል፡፡
 
የስልጠና አሰጣጣቸውም በፅሁፍና በተንቀሳቃሽ ምስል የተደገፈ በመሆኑ ተሳታፊዎች ስልጠናው ጥሩና ደረጃውን የጠበቀ መሆኑን ገልፀው በርካታ ነገር መቅሰማቸውን ተናግረዋል፡፡ አሰልጣኙ ባቀረቧቸው ፅሁፎች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዶ ለተነሱት ጥያቄዎች መልስ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዩች ም/ፕሬዘዳንት ዶ/ር እሰይ ከበደ በማጠቃለያ ንግግራቸው ፕሮፌሰር ዳንኤል ቅጣው ወርቃማ ጊዜአቸውን ሰጥተው ይህን ዘርፈ ብዙ ስልጠና በመስጠታቸው ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበው ዩኒቨርሲቲው ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቀጥሎ በሁለተኛ ደረጃ እንደሚገኝ አውስተው ካለው ከፍ ብሎ ለመገኘት ከስርዓተ ትምህርቱ ጀምሮ ጥራት ያለው ስራ በማከናወንና ከሌሎች ቀድሞ በመገኘት እንዲሁም ተማሪዎች መርጠው እንዲመጡ ለማድረግ ሁሉም ከስልጠናው ያገኘውን ክህሎት ወደ ተግባር እንዲለውጥ በአደራ መልኩ አሳስበዋል፡፡
በሙሉጎጃም አንዱዓለም
 
 

BDU Staff from Three Faculties took part in Pre-doctoral and Post-doctoral Research and Writing Workshop in the Netherlands, The Hague and Amsterdam

Seven BDU Staff from the Faculty of Social Sciences, Humanities, and Law school participated in an Interdisciplinary and intensive pre-doctoral and post-doctoral research and writing workshop held for 10 days (June 27 to July 6/ 2022) in the Netherlands,. The workshop, held at the International Institute of Social Studies (ISS), The Hague, and VrijeUniversiteit Amsterdam in Amsterdam, comprised a wide range of activities, including presentations and feedbacks on pre-doctoral and post-doctoral research projects, specialized training sessions on the research process, techniques of literature search and review, use of references managers, framing of arguments, writing and publications and several other subjects on research, scientific writing and publication.

The workshop was organized as part of a series of activities of the Law, Democratization and Media (LA-DEM-MED- visit: https://la-dem-med.et for more on the project) Project of which BDU is currently taking part as a member of a wider consortium of local and Dutch academic institutions which, among others, includes the International Institute of Social Studies (ISS) and VrijeUniversiteit Amsterdam. The event also included visits to the library systems and institutional facilities of these two high ranking higher education institutions in the Netherlands.

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ዩኒቨርሲቲዉን ወክሎ የአማራ ሊግ የእግር ኳስ ውድድር ላይ ለሚሳተፈው ልዑካን ሽኝት አደረገ

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ በስሩ አቅፎ ለያዛቸዉ 8 የሚሆኑ የተለያዩ የስፖርት ፕሮጀክት ሰልጣኞች መካከል አንዱ የሆነዉን ከ20 አመት በታች የእግር ኳስ ፕሮጀክት የአማራ ሊግ የእግር ኳስ ውድድር ላይ እንዲሳተፍ ወደ ከሚሴ ከተማ ሸኝቷል፡፡

 የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ባህልና ስፖርት መምሪያ ባካሄደዉ የ2014 ዓ.ም የክለቦች ውድድር ላይ እንዲሳተፍ በማድረግ የዩኒቨርሲቲዉ የእግር ኳስ ክለብ ለዋንጫ ጨዋታ በማለፍ 2ኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ የአማራ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን በሚያወዳድረዉ የአማራ ሊግ የእግር ኳስ ውድድር ላይ ዩኒቨርሲቲዉን እና ከተማ አስተዳደሩን ወክሎ በከሚሴ ከተማ ከሀምሌ 02-21/2014 ዓ.ም ድረስ በሚካሄደዉ ክልል አቀፍ የክለቦች ውድድር ላይ ለመሳተፍ በመመረጣቸዉ ከሀምሌ 01/2014 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ከሚሴ ከተማ አቅንቷል፡፡

 የዚህ ዉድድር ዋና አላማ ወደ አማራ ሊግ የሚገቡ ክለቦችን መለየት ሲሆን የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የእግር ኳስ ክለብ ዉጤታማ ሆኖ ወደ አማራ ሊግ እንዲገባ ለማስቻል መሆኑን የስፖርት አካዳሚው ዲን የሆኑት ዶ/ር ዳኛቸዉ ንግሩ ተናግረዋል፡፡

ዶ/ር ዳኛቸዉ ባስተላለፉት መልዕክት ባሕር ዳር ከተማ ላይ በተካሄደዉ የእግር ኳስ ውድድር ያስመዘገቡትን አበረታች ዉጤት አጠናከረዉ እንዲቀጥሉ አሳስበዋል፡፡ ለሁሉም ተወዳዳሪዎች ሙሉ የስፖርት ቱታ ሽልማት በማድረግ ለዚህ ዉድድር እንዲበቁ ላደረጉ የአካዳሚዉ አሰልጣኞች እና መምህራን እንዲሁም ድጋፍ ላደረጉ የዩኒቨርሲቲዉ ከፍተኛ አመራሮች በማመስገን እና መልካም ዉጤት በመመኘት ተጫዋቾችን ሸኝተዋል፡፡

መልካም ዉጤት ለዩኒቨርሲቲዉ የእግርኳስ ክለብ!

ትላልቅ የድንች ዘርን ከታትፎ በማከም መዝራት የድንች ምርትን እንደሚያሳድግ ተጠቃሚ አርሶ አደሮች ተናገሩ

(ሰኔ 29/2014 ዓ.ም፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-BDU) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ለድንች ምርት ምቹ በሆነው የይልማና ዴንሳ፣ ቋሪት እና ሰከላ አዋሳኝ በሆነው ብር አዳማ አካባቢ ለሚኖሩ አርሶ አደሮች ትላልቅ የድንች ዘርን ከታትፎ በማከም መዝራትና የድንችን አበባ በመቀንጠብ የድንች ምርት የመጨመር እና ዘርን የመቆጠብ  ቴክኖሎጂን አስመልክቶ ስልጠናውን ወሰደው ማሳቸውን በዘር የሸፈኑ አርሶ አደሮችን ማሳ በዩኒቨርሲቲው የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር ዶ/ር ነፃነት በየሮ የተመራ የባለሙያዎች ቡድን ምልከታ አድርጓል፡፡

በመስክ ምልከታው ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር ዶ/ር ነፃነት በየሮ እንዳሉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማር ጎን ለጎን የህብረተሰቡን ችግር ሊፈታ የሚችል የምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎችን እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በቋሪትና  በይልማና ዴንሳ ወረዳዎች በፈንገጣ፣ በስም አረጋ እና ብር አዳማን ጨምሮ በሌሎችም ቀበሌዎች ከተፈጥሮ ሐብት ጥበቃ ጀምሮ የወተት ምርትን ሊጨምሩ የሚችሉ የላሞችን እና በጎችን ዝርያ የማሻሻል፣ ትምህርት ቤቶችን የመደገፍ እና ለአርሶ አደሩ ነፃ የህግ አገልግሎት የመስጠት ስራዎችን በስፋት እየሰራ እንዳለ በመስክ ምልከታው ላይ ተናግረዋል፡፡

በዕለቱ  ትላልቅ  የድንች ዘርን  በመከታተፍ መዝራትና የድንችን አበባ በመቀንጠብ ምርት እና ምርታማነትን የመጨመር ቴክኖሎጂን አስመልክቶ  ስልጠና የወሰዱ አርሶ አደሮች የወሰዱትን ስልጠና በጥሩ ሁኔታ በመተግበራቸው በማሳቸው ላይ የተሻለ  የድንች ሰብል በማየታቸው መደሰታቸውን ተናግረው ሌሎች የአካቢው አርሶ አደር ቴክኖሌጅውን በስፋት በመጠቀም የድንች ምርትን  ማሳደግ እንደለባቸው ተናግረዋል፡፡

በይልማና ዴንሳ ወረዳ የስም አረጋ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ቻሌ አለሙ እና በቋሪት ወረዳ ፈንገጣ ቀበሌ ነዋሪ እና የቴክኖሎጂው ተጠቃሚ  የሆኑት አርሶ አደር ሞላ አዘነ እንዳሉት አካባቢው በከፍተኛ ደረጃ ድንች አምራች በመሆኑ አርሶ አደሩ ካለው መሬት ላይ ሃምሳ በመቶውን በድንች ሰብል ስለሚሸፍን የዘር እጥረት እንደሚያጋጥማቸው ተናግረዋል፡፡ አሁን ላይ ግን የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ያመጣውን  ቴክኖሎጂ ተጠቅመን ትላልቅ የድንች ዘርን በመከታተፍ እና በማከም ዘርተው የዘር እጥረቱን ማስቀረት መቻላቸውን ተናግረው  አበባውን በመቀንጠብ ምርቱን እንዲጨምር የማሳ እንክብካቤ በማድረግ የዘሩት ዘር በሙሉ በማሳው ላይ በማየታቸው የሚሰጠውን ውጤት በጉጉት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል፡፡ ሌሎች የአካባቢው አርሶ አደሮች ቴክኖሎጂውን ለመጠቀም ከፍተኛ ተነሳሽነት አንዳሳደረባቸው ተጠቀሚ አርሶ አደሮች አክለው ተናግረዋል፡፡

ከመስክ ምልከታው በኋላ አርሶ አደሮች በትግበራው ወቅት ያጋጠሟቸውን ችግሮች እና ሌሎች አርሶ አደሮች የቴክኖሎጂው ተጠቃሚ ለመሆን የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች መሰርት አድርጎ ውይይት ተደርጓል፡፡ በመስክ ምልከታው ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የውስጥ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ግርማው አሽብርን ጨምሮ በማሕበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር ስር የሚሰሩ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

Thank YOU for visiting and inviting our pages, for your likes and shares!

ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:- https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

 

የማህበራዊ ሳይንስ ፋኩልቲ የ2014 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሄደ
*************************************************************************
(ሰኔ 29/2014 ዓ.ም፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-BDU)
የማህበራዊ ሳይንስ ፋኩልቲ የ2014ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2015 የትምህርት ዘመን ዕቅድ ላይ የማጠቃለያ ውይይት በቀድሞው የሴኔት መሰብሰቢያ አዳራሽ አካሄደ፡፡
ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የማህበራዊ ሳይንስ ፋኩልቲ ዲን ዶ/ር ታዬ ደምሴ በሪፖርታቸው ሳይታቀዱ የተከናወኑ፣ ታቅደው ያልተከናወኑ፣ ያጋጠሙ ዋና ዋና ችግሮች እና በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ለመፈፀም የተቀመጡ ዋና ዋና ተግባራትን በማቅረብ ፋኩልቲው በ6 የትምህርት ክፍሎች፣ በ12 ቅድመ ምረቃ፣ በ14 ድህረ-ምረቃና በ7 የሶስተኛ ዲግሪ በድምሩ 33 ፕሮግራሞች መኖራቸውን ገልፀዋል፡፡
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ በመርሃ-ግብሩ ላይ ዩኒቨርሲቲው በማሪታይም፣ በኢንጅነሪንግ እና በቴክስታይል በውጤታማነት የተጓዘባቸውን ርቀት ለታዳሚው አስታውሰዋል፡፡ ዶ/ር ፍሬው ከመምህራን ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጡ አሁን ያለውን ወቅታዊ ችግርበመገንዘብ ምሁራንም ግጭቶችን ለማስቀረት የሚጠበቅባቸዉን ሚና እንዳልተወጡ እና ዩኒቨርሲቲው በሚቀጥለው አመት የሚያከብረውን 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንደ መልካም አጋጣሚ የመጠቀም ክፍተት እና ወረቀቶችን በማሳተም የሚፈለገውን ያህል አለመሰራቱን በውይይቱ አንስተዋል፡፡
በመጨረሻም በመምህርነት፣ በምርምር፣ በማህበረሰብ አገልግሎት፣ በስራ መሪነት፣ በአስተዳደር ሰራተኛ የተሻለ አፈጻፀም ላስመዘገቡ የዕውቅና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU
ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ
Wisdom at the source of Blue Nile
Thank YOU for visiting and inviting our pages, for your likes and shares!
ለተጨማሪ መረጃዎች፡-
Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official
website :- www.bdu.edu.et
የመሬት አስተዳደር ተቋም በከተማ መሬትና ፕላን ዘርፍ እየሰጠ የነበረውን ስልጠና አጠናቀቀ
=============================================
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመሬት አስተዳደር ተቋም ከከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የከተሞች ገቢ ሪፎርም ፕሮጀክት ጽ/ቤትጋር በመተባበር በከተማ መሬትና ፕላን ዘርፍ በተዘጋጁ የሙያ ደረጃዎች ማለትም ከደረጃ II እስከ V ለማሰልጠን እና የሙያ ብቃት ምዘና (COC) ለመመዘን የሚያበቃ ስልጠና ከግንቦት 22 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በመሰጠት ላይ የነበረው ስልጠና የማጠቃለያ መርኃ-ግብር በ28/10/14 ዓ.ም በጥበብ ህንፃ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሄደ::
ፕሮግራሙን በንግግር የከፈቱት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ ለመሬት አስተዳደር ተቋም ልዩ ትኩረት እንዳላቸው አውስተው በአገር አቀፍ ደረጃ በሙያው የካበተ ልምድ ያላው የተማረ የሰው ኃይል በብዛት ባለመኖሩ ዩኒቨርሲቲው ሰፊ ስራ መስራቱንና በትክክል በሙያው ባለቤቶች የተደጋጀ ተቋም መመስረቱን ተናግረዋል፡፡
ፕሬዘዳንቱ በማስከተል ተቋሙ ከተመሰረተ አጭር ጊዜ ቢሆንም ከ1ኛ እስከ 3ኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ተቀብሎ በማሰልጠን ደረጃ ያለና ዩኒቨርሲቲውን በልዩነት ከሚያስጠሩት ፕሮግራሞች አንዱ መሆኑን ገልፀው ተመርቀው የሚወጡት ተማሪዎችም ከሌሎች ሙያዎች በተሻለ መልኩ የስራ እድል እያገኙ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በተጨማሪም መሬት አንዱ የሙስና ዋሻ ስለሆነ የአሰራር ስርዓቱን ለማዘመን ስልጠናው ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ፕሬዘዳንቱ አስገንዝበዋል፡፡
የዕለቱ የክብር እንግዳና የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ፈንታ ደጀን በበኩላቸው ለሰልጣኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውንና ዩኒቨርሲቲው በግንባር ቀደምትነት ላበረከተው አስተዋፅኦ ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበው ስልጠናው የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን ለማዘመን ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የክብር እንግዳው አክለውም በአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ የከተሞች መስፋፋት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ ለህዝቡ አስፈላጊውን የመሰረተ ልማት አውታር በአንድ ጊዜ መዘርጋት አዳጋች መሆኑን አስገንዝበው የከተማ መሬት አስተዳደርን በተለምዶ ከሚሰራበት የአሰራር ስርዓት አላቆ በአዲስ መልክ በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር በማከናወን የማህበረሰቡን ፍላጎት ያሟላ ስራ እንዲሁም የነበረውን ክፍተት በመሙላት ሰልጣኞች ከስልጠናው መልስ የእውቀት ሽግግር አድርገው ለሌሎች የቀሰሙትን ክህሎት በማካፈል ከታችኛው እርከን ድረስ በመውረድ ስራ እንዲሰሩ በአንክሮ አሳስበዋል፡፡
የሰልጣኞች ተወካይና ከአብክመ የከተሞች ፕላንና ልማት ኢንስቲትዩት የቅየሳ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ወይዛዝርት አሞኘ የስልጠናውን ደካማና ጠንካራ ጎን አሳይተው በርካታ ጠንካራ ጎኖች የታዩ መሆኑንና መሻሻል ያለበት የስልጠናው ጊዜ ማጠሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በመርኃ ግብሩ ላይ ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍል የተውጣጡ የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን ለሰልጣኞች የስራ መመሪያ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ሰልጣኞች ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍል የተውጣጡና በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ማለትም Cadastral Surveying and Mapping, Cadastral Registry System, Urban Planning and Land Administration እና Real Property Valuation በተሰኙት የሙያ ዘርፎች165 ሰልጣኞች የሰለጠኑ ሲሆን 39 ሴቶች መሆናቸው እንዲሁም በሌሎች አራት ዩኒቨርሲቲዎች፡-ሲቪል ሰርሲስ፣ድሬዳዋ፣አምቦና ወላይታ ሶዶ በተመሳሳይ መልኩ ስልጠናው መሰጠቱ ተገልፆ ለአራቱ የቡድን ተወካዮች የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡
በማጠቃለያውም ከሙያ ብቃት ምዘና (COC) የስራ ዘርፍ በመጡ ባለሙያዎች ሰልጣኞች ለመመዘን የሚስችላቸውን እውቀት እንዳገኙና የምዘናውን አሰጣጥ ስርዓት የግንዛቤ ማስጨበጫ ገለፃ ተደርጓል፡፡
በሙሉጎጃም አንዱዓለም
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲና የደህንነት ጥናት ተቋም "አገራዊ ምክክር ለኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል የጋራ ጉባኤ አካሄዱ
*************************************************************************
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲና የደህንነት ጥናት ተቋም (Institute for Security Studies /ISS/) በጋራ በመተባበር አገራዊ ምክክር ለኢትዮጵያ፤አስፈላጊነት ፣ሂደት፣ የባለድርሻ አካላት ሚና እና የቢሆን ትንታኔዎች ላይ ያተኮረ የጋራ ጉባዔ በ22/10/14 በባሕር ዳር ከተማ ኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓ አካሄደ።
የጉባኤውን መከፈት ያበሰሩት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ መረሃ- ግብሩን ላዘጋጁት አካላት ምስጋና እና ከሩቅም ከቅርብም ጉባኤውን ለመታደም ለመጡት ተሳታፊዎችና የፅሁፍ አቅራቢዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው ጉባኤው ወቅቱን ያማከለ መሆኑንና አገራችን ኢትዮጵያን ካጋጠማት ተግዳሮት ለማውጣት አካታች ብሔራዊ ምክክር ማድረጉ ይበል የሚያሰኝ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ አክለውም አገራችን ኢትዮጵያ የብዝሃ ብሔርና ሐይማኖት ባለፀጋ መሆኗን አውስተው እነዚህ እሴቶች ለዕርስ በርዕስ መግባቢያነት እንዲሁም አንድነት ለማጠናከር የሚያግዙ ቢሆንም ከጊዜ ወደጊዜ የግጭት መንስኤ እየሆኑ በመምጣታቸው አንድነትን ለመፍጠር እንዲሁም በተለያዩ ጊዜያት የሚከሰቱትን የፖለቲካ መካረር ለማለዘብ የጉባኤው ፋይዳ የጎላ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
በተጨማሪም አገራችን ኢትዮጵያ ከገባችበት አዘቅት ለማውጣት የምሁራኑ ሚና ወሳኝ በመሆኑ በጉባኤው ጥልቅ ውይይት እንደሚካሄድና የወደፊት የትኩረት አቅጣጫ ተለይቶ መሬት የነካ ተግባር እንደሚከናወን ፕሬዚዳንቱ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል፡፡
የጉባኤው ዓላማ የአገራዊ ምክክር ምንነትና ያለውን ጠቀሜታ፣አነሳሽ የሆኑ ገፊ ምክንያቶች እንዲሁም የተሳካ አገራዊ ምክክር በኢትዮጲያ ለማካሄድ ሊሟሉ የሚገባቸው ምቹ ሁኔታዎች ላይ ግንዛቤ ለማስጨበጥ፣ትክክለኛ አካታችና ፍትሃዊ ብሔራዊ ምክክር ተግባራዊ እንዲሆን ባለድርሻ አካላት ያላቸውን ሚና ማሳወቅ እንዲሁም ምክክሩ ውጤታማ ቢሆን የሚገኘው ሀገራዊ ትርፍ፣ካልሆነ ደግሞ ሊያስከትል የሚችለውን ሀገራዊ ኪሳራ ለማመላከት ነው፡፡
ለምክክሩ መነሻ የሚሆን ፅሁፍ ያቀረቡት ምሁራን ከደህንነት ጥናት ተቋም ዶ/ር ሰሚር የሱፍ
"የአገራዊ ምክክር አስፈላጊነት በታሪካዊ እና ንፅፅራዊ እይታ" በሚል ርዕስ፣ ዶ/ር አደም ካሴ ከ IDEA International ባሉበት ስፍራ በበይነ መረብ "ለተሳካ አገራዊ ምክክር አስፈላጊ ሁኔታዎች በሚል ርዕሰ ጉዳይ፣ በወ/ሮ ሰብለ ሃይሉ "ለአገራዊ ምክክር የባለድርሻ አካላት ሚና" በሚል ርዕስ እና ፕሮፌሰር ሹመት ሲሻኝ "ኢትዮጵያ ከስኬታማ አሊያም ከተሰናከለ አገራዊ ምክክር በኋላ፤ምጥን የቢሆን ትንተናዎች በተሰኘ ርዕስ አቅርበዋል፡፡
በጉባዔው ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍል የተውጣጡ የመንግስት ስራ ኃላፊዎች፣የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣መምህራንና ፕሮፌሰሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የሀይማኖት አባቶች የተገኙ ሲሆን በቀረቡት ፅሁፎች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሄዶ ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የጉባኤውን አንኳር ሀሳቦችና ጎልተው የወጡትን ነጥቦች ያቀረቡት የደህንነት ጥናት ተቋም ተመራማሪና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት አቶ ተግባሩ ያሬድ በአሁኑ ወቅት አገራችን ኢትዮጲያ ጊዜ የማይሰጠው ተግዳሮት እንዳጋጠማትና አገራዊ ምክክር ደግሞ የግጭት ማስተዳደሪያ መሳሪያ ስለሆነ ያለፈውን የታሪክ ትርክት የሚታይበትና የወደፊት የትኩረት አቅጣጫ የሚለይበት ግንዛቤ መፈጠሩን ገልፀዋል፡፡
በማስከተልም ታሪክ ቀመስ ችግሮችን ምሁራኑ ተረባርቦ በተቋም ደረጃ እንዲሁም የሐይማኖት ተቋማትን ጨምሮ ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የተዛባውን አካሄድ በመመለስ የሀገራችንን ህልውና ወደ ነበረበት ሁኔታ ማስተካከል ተገቢ መሆኑ በሰፊው መወሳቱን ተናግረዋል፡፡
የወደፊት የትኩረት አቅጣጫ ሲለይ የተነሱት በርካታ ጉዳዮች ቢሆኑም ለአገራዊ ምክክር "አባይን በጭልፋ" አይነት ስለሆነ በተለይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በስሩ በርካታ ምሁራን ስላሉ ጥበብ በተሞላበት መንገድ አገርን መታደግ እንደሚቻልና ምክክሩ ቀጣይነት እንዲኖረው ፕሮፌሰር ያለው እንዳወቀን ጨምሮ የጉባኤው ተሳታፊዎች ተናግረዋል፡፡
የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የክብር እንግዳው አቶ ክቡር ገና ለፕሮግራሙ አዘጋጆች፣ ለፅሁፍ አቅራቢዎችና ለተሳታፊዎች ምስጋና አቅርበው የሰላሙ ጉዳይ እልባት ያጣው የደከመ ሀሳብ ተሸክመን እየሄድን ስለሆነ ነው ብለዋል፡፡
ለዚህም መፍትሄው ይላሉ በማስከተል አቶ ክቡር አገራዊ ምክክር ሲካሄድ የአሸናፊና የተሸናፊ አይነት ውይይት ሳይሆን ሁሉም በተመሳሳይ አዲስ ሀሳብ ላይ ጥበብ በተሞላበት ሁኔታ መወያየት ከቻለ ዘላቂ መፍትሄ ማምጣት እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡
አቶ ክብሩ አክለውም ምክክሩ የምሁራኑን ሚና አካቶ መቀጠል እንዳለበትና ከታለመው ግብ ለመድረስ ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የበኩላቸውን መወጣት እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡
 
በሙሉጎጃም አንዱዓለም

Pages