Latest News

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከዓለም አቀፍ የእንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት (International Livestock Research Institute) /ILRI/ጋር የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከዓለም አቀፍ የእንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት (International Livestock Research Institute) /ILRI/ ጋር አብሮ ለመስራት በፕሬዘዳንት ጽ/ቤት በ19/12/14 ዓ.ም. የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው ዩኒቨርሲቲው ከምስረታው ጀምሮ አሁን እስከ ደረሰበት ደረጃ ያለውን ዋና ዋና ሂደት፣ራዕዩን፣ተልዕኮውን እና በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያሉ ፕሮግራሞች እንዲሁም የሰው ኃይሉን አጠቃላይ እያከናወነ ያላቸውን አኩሪ ተግባራት የሚያሳይ ፅሁፍ አቅርበዋል፡፡

የዓለም አቀፍ የእንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት (International Livestock Research Institute) (ILRI) ዋና ዳይሬክተር Dr. Jimmy Smith ተቋማቸውን የሚያስተዋውቅ ፅሁፍ አቅርበዋል፡፡

የስምምነት ሰነዱን የተፈራረሙት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘና የዓለም አቀፍ የእንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር Dr. Jimmy Smith ሲሆኑ ከዓለም አቀፍ የእንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት የመጡት ልዕክና የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ቤተ-ሙከራዎችን ጨምሮ ምን እንደሚመስል እንዲሁም የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና የጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝ ሆስፒታል በስፋት ጎብኝተዋል፡፡

የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዳይሬክተር በሆኑት በፕሮፌሰር የሽጌታ ገላው መሪነት ኮሌጁ ሲጎበኝ በቅርቡ ስራ የሚጀምረውና በአገር አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሰው ጣና የምርምርና ዳያግኖስቲክ ማዕከል የተሰኘው በውስጡ 237 ክፍሎችን የያዘ ሲሆን ለወደፊት በርካታ ችግር ፈች የምርምር ዘርፎች የሚከናወኑበት መሆኑን ከጉብኝቱ ለመረዳት ተችሏል፡፡

በዚሁ ኮሌጅ በቀድሞ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ዶ/ር ባይሌ ዳምጤ ስም የተሰየመውን ዘመናዊ ቤተ-መፅሓፍት፣ ንፁህ የተማሪዎች መመገቢያ አዳራሽ፣ በዚህ ዓመት የሚመረቁት 160 ሐኪሞች የሚኖሩበት ዶርሚተሪ እና የመሳሰሉት ዋና ዋና የስራ ክፍሎች ተጉብኝተዋል፡፡

በሙሉጎጃም አንዱዓለም

 

 

 

 

 

 

A team of delegates from International Livestock Research Institute (ILRI) led by Dr. Jimmy Smith, pays a visit to College of Medicine and Health Sciences.

==========================================================

(August 26 ,2022, Bahir Dar): A team of delegates from International Livestock Research Institute (ILRI) led by Dr. Jimmy Smith, Director General of the institute, paid a visit to College of Medicine and Health Sciences.

The team visited Tana Research and Diagnostic Center(TRDC) with the aim of assessing possible areas of collaboration in animal health and nutrition.

During the visit, Prof. Yeshigeta Gelaw, Chief Executive Director of the college provided brief explanations about the center in particular and the college at large.

They also visited the overall physical infrastructure of the college.

Before the visit, the institute had signed a Memorandum of Understanding ( MoU) with Bahir Dar University.

 

 

የተለያዩ የፈጠራ ስራ ውጤቶች የታዩበት ዓውደ ርዕይ ተካሄደ

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር የተሻለ የፈጠራ ስራ ያስመዘገቡ ስራ ፈጣሪዎች የተሳተፉበት ለሶስት ተከታታይ ቀናት የቆየ ዓውደ ርዕይ  በባሕር ዳር የወጣቶች ሳይንስ ካፌ አካሄደ፡፡

በዓውደ ርዕዩ ላይ የተሳተፉት በባሕር ዳር ከተማ የሚገኙ የተሻለ የፈጠራ ውጤት ያስመዘገቡ ትምህርት ቤቶችና ከተለያዩ ቦታ የመጡ ተሳታፊዎች ስራቸውን ያቀረቡ ሲሆን የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስቴም ሴንተር፣ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት እና ኢንተርፕርነር ዴቨሎፕመንት ተጠቃሽ ሲሆኑ ዩኒቨርሲቲው ሌሎችን በማስተባበር አውደ ርዕዩ እንዲካሄድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡

የአብክመ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ሳሌ አያሌው ያደጉት አገራት ለሳይንስና ቴክኖሎጂ ትኩረት በመስጠታቸው ለእድገት በር ከፋች እንደሆነላቸው አውስተው በእኛ አገር ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ሳይንስና ተክኖሎጂ ሊሰጠው የሚገባው ትኩረት ተነፍጎት እንደቆየና አሁን ላይ የቀጣይ የትኩረት አቅጫ ሆኖ ይሰራበት ዘንድ የአውደ ርዕዩ መካሄዱ የፈጠራ ስራዎችን ለማስተዋወቅ አንድ ርምጃ የሚያስኬድ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ኮሚሽነሩ በማስከተል የፈጠራ ውጤት ባለቤቶች እንዲበረታቱና ወደ ማምረት ገብተው የኩባንያ ባለቤት የሚሆኑበት መንገድ ቢመቻች በውጭ ምንዛሬ ወደ አገራችን የሚገባውን ለማስቀረትና ወደ ውጭ በመላክ የአገሪቷን ኢኮኖሚ ማሳደግ እንደሚቻል አስገንዝበው ይህ ተግባር እውን የሚሆነው በመንግስትና በማህበረሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎ በመሆኑ ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ርብርብ ማድረግ እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡

በሶስት ቀን ቆይታው በፖሊሲው ዙሪያ የመንግስት ከፍተኛ አመራሮችና የፈጠራ ባለሙያዎች የተሳተፉበት ውይይቶች የተካሄዱ ሲሆን በፈጠራ ስራ የተሻለ ልምድ ያላቸውና ውጤታማ የሆኑ ሰዎች ልምዳቸውን ለተሳታፊዎች አቅርበዋል፡፡ አቅራቢዎችም ቁልፍ የስኬት መንገዶችን በዝርዝር ተናግረው ሁሉም ባለው አቅም በይቻላል መንፈስ ከሰራ ውጤታማ መሆን እንደሚቻል አስገንዝበዋል፡፡

ለአውደ ርዕዩ ተሳታፊዎች የምስክር ወረቀት የተሰጠ ሲሆን አጠቃላይ 25 የሚደርሱ ተሳታፊዎች የፈጠራ ውጤታቸውን በማቅረብ ስራቸው ተገምግሞ ከ1-5ኛ ለወጡት ማለትም 1ኛ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስቴም ሴንተር፣ 2ኛ SOS School፣ 3ኛ ድልችቦ ትምህርት ቤት፣ 4ኛ እሸት አካዳሚ፣ 5ኛ RISPINS INTERNATION SCHOOL ተሳታፊዎች ለእያንዳዳቸው ሁሉን ያሟላ የቴክኖሎጂ መስሪያ ቁሳቁስ (Since Kite) ተበርክቶላቸዋል፡፡ ሽልማቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በምርምሩ ዘርፍ የሚሰሩት አቶ ታደሰ አንበሴ እና የአብክመ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር አቶ መላኩ ጥላሁን አበርክተዋል፡፡

አውደ ርዕዩ የአብክመ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን ከ2015 ዓ.ም እቅድ መካከል አንዱ እንደሆነና ጠቀሜታውም ለተሳታፊዎች የዕርስ በዕርስ ትውውቅና የእያንዳንዱ የፈጠራ ስራ በአእምሮአዊ ንብረት እንዲመዘገብ ማገዙን አቶ መላኩ ጥላሁን ገልፀዋል፡፡ አክለውም በአሁኑ ወቅት ለአገሪቱ አስፈላጊ የትኩረት አቅጣጫ የሆነው ሳይንስና ቴክኖሎጂ ስለሆነ ዩኒቨርሲቲዎችና ኢንዱስትሪዎች ተናበው በመስራት የፈጠራ ባለቤቶችን የሚያግዝ ስራ ከስርዓተ ትምህርት ቀረፃ ጀምሮ በመስራት ቴክኖሎጅውን ማስረፅ ተገቢ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ዶ/ር ሳሌ የኑሮ ውድነትን ለመቅረፍና የፈጠራ ባለቤቶችም ትኩረት አግኝተው በስራቸው አእምሯዊ ንብረት በማስያዝ ከባንክ የገንዘብ ብድር ተመቻችቶላቸው ስራቸውን በሰፊው እንዲያከናውኑና አምራች ድርጅት እንዲያቋቁሙ የሚያግዝ ፖሊሲ ተቀርፆ ስራ ላይ ማዋል እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ- ባዳዩ-BDU

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

Thank you for Inviting, like, share & visiting BDU page!

ለተጨማሪመረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:-https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

 

General List of PhD Programs at BDU: Possible areas of collaboration for all disciplines:

  1. College of Education and Behavioral Sciences
    1. Doctor of philosophy in Curriculum and Instruction
    2. Doctor of philosophy in Educational Policy and Leadership
    3. Doctor of philosophy in Educational Psychology
    4. Doctor of Philosophy in Higher education Leadership and Management
  2. College of Agriculture and Environmental Sciences
    1. Doctor of philosophy in Agronomy
    2. Doctor of philosophy in Fisheries and Wetlands Management
    3. Doctor of philosophy in Applied Soil Science
    4. Doctor of philosophy in Animal Genetics and Breeding
    5. Doctor of philosophy in Animal Nutrition
  3. College of Business and Economics
    1. Doctor of philosophy in Economics
    2. Doctor of philosophy in Accounting & Finance
    3. Doctor of philosophy in Management
  4. Faculty of Social Sciences
    1. Doctor of philosophy in Geography & Environmental Studies
    2. Doctor of philosophy in History
    3. Doctor of philosophy in Political science and international studies
  5. Faculty of Humanities
    1. Doctor of philosophy in Teaching English as a Foreign Language
    2. Doctor of philosophy in Literature
    3. Doctor of philosophy in Teaching Amharic
    4. Doctor of philosophy in Media and Communication
  6. Institute of Land Administration
    1. Doctor of philosophy in Land policy and governance

 

  1. School of Law
    1. Doctor of philosophy in Law
  2. College of Science
    1. Doctor of philosophy in Mathematics (Algebra, Applied Mathematics)
    2. Doctor of philosophy in Mathematics Education
    3. Doctor of philosophy in Space Physics
    4. Doctor of philosophy in Atmospheric Physics              
    5. Doctor of philosophy in Solid State Physics      
    6. Doctor of philosophy in Plant Biology
    7. Doctor of philosophy in Applied Microbiology
    8. Doctor of philosophy in Biomedical Sciences
    9. Doctor of philosophy in Statistics
    10. Doctor of philosophy in Analytic Chemistry
    11. Doctor of philosophy in Biotechnology(Health, Agricultural, Environmental and Industrial)

 

  1. Sport Academy
    1. Doctor of philosophy in Sport Science (Coaching Athletics)
    2. Doctor of philosophy in Sport Science (Coaching Volley Ball)
    3. Doctor of philosophy in Sport Science (Coaching Foot Ball)
  2. College of Medicine and Health Sciences

Masters

  1. Master of General Public Health
  2. Master of Public Health in Water, Sanitation and Hygiene
  3. Reproductive Health
  4. Master of Public Health in System and Project Management
  5. Master of Public Health in Epidemiology
  6. Master of Public Health in Field Epidemiology
  7. Master of Public Health in Health Promotion
  8. Master of Public Health in Public Health Nutrition
  9. Master of Science in Medical Microbiology
  10. Master of Science in Medical Parasitological
  11. Master of Science in Clinical Midwifery
  12. Master of Science in Integrated Emergency Surgery
  13. Master of Science in Integrated Clinical & Community Mental Health
  14. Master of Science in Adult Nursing
  15. Master of Science in Pediatrics Nursing

PhD

  1. Doctor of philosophy in Public Health
  2. Doctor of Philosophy in Human Nutrition
  3. Doctor of Philosophy in Environmental Health
  4. Doctor of Philosophy in Reproductive Health

Specialty

  1. Specialty in Surgery
  2. Specialty in Radiology
  3. Specialty in Gynecology and Obstetrics
  4. Specialty in Internal medicine
  5. Specialty in Orthopedics and Trauma Management
  6. Specialty in Pediatrics
  7. Specialty in Dermatology
  1. Bahir Dar Institute of Technology
    1. Doctor of philosophy in Sustainable energy engineering
    2. Doctor of philosophy in Electrical Power  Engineering
    3. Doctor of philosophy in Postharvest technology
    4. Doctor of philosophy in Chemical engineering (Process Engineering and Design)
    5. Doctor of philosophy in Chemical engineering (Environmental & Biological Engineering)
    6. Doctor of philosophy in Chemical engineering (Biochemical Engineering)
    7. Doctor of philosophy in Chemical engineering (Polymer Science and Engineering)
    8. Doctor of philosophy in Chemical engineering (Industrial and Environmental Biotechnology)
    9. Doctor of philosophy in Chemical engineering (Nano Science and Technology )                
    10. Doctor of philosophy in Agricultural Mechanization engineering
    11. Doctor of philosophy in Industrial and Systems Engineering
    12. Doctor of philosophy in Mechanical engineering ( Mechanical Design)
    13. Doctor of philosophy in Mechanical engineering  (Manufacture Engineering)
    14. Doctor of philosophy in Mechanical engineering  (Thermal Engineering)
    15. Doctor of philosophy in Civil engineering (Construction engineering and management)
    16. Doctor of philosophy in Water resources engineering and management
  2. Institute of Textile and Fashion Technology
    1. Doctor of philosophy in Textile Technology
    2. Doctor of philosophy in Fashion  Technology

ብሉ ኢኮኖሚ ዙሪያ አውደ ጥናት ተካሄደ

***********************************

[ነሐሴ 13/2014ዓ/ም፤ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ -ባዳዩ]  የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የብሉ ኢኮኖሚ የልህቀት ማዕከል ሆኖ የጣና ሀይቅን እና የውሃ ሃብትን ለዘላቂና ለአካባቢ ተስማሚ ልማት እንዴት መጠቀም እንዳለብን ትኩረት ሰጥቶ ለመስራት የሚያስችል ውይይት በምስራቅ አፍሪካ ብይነ መንግስታት የዘላቂ አካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ ባለሙያዎች በተገኙበት በጥበብ አዳራሽ አውደ ጥናት አካሄደ።

ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ እንደገለጹት የአውደ ጥናቱ አላማ ብሉ ኢኮኖሚ በሚባለው ፅንሰ ሀሳብ ላይ ግልፅነት መፍጠር ሲሆን የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ስራዎችን በውሃ ዙሪያ ትኩረት በማድረግ ብሉ ኢኮኖሚ ላይ በስፋት በመስራት ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ያሉትን ጸጋዎች ማለትም በአገሪቱ ብቸኛውን የኢትዮጵያ የባህር ሃይል ወይም ማሪታይም ተቋም ከፍቶ ሙያተኞችን በማሰልጠን፤ የብሉ ናይል ውሃ ምርምር ተቋም፣ ዓሣ ትምህርት ክፍል፤ ቱሪዝም ትምህርት ክፍል፤ ኢንጅነሪግ ትምህርት ክፍሎችን ከፍቶ በማስተማር እና በመመራመር ለአገራችን የብሉ ኢኮኖሚ እድገት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ ያብራራሉ፡፡

ዶ/ር ፍሬው አክለውም የጣና ሀይቅ የቱሪስት መስህብ በመሆን፤ በርካታ ቱሪስቶችን በመቀበል በሚሰጠው ጠቀሜታ እንዲሁም ለአካባቢ ጥበቃ ካለው ትልቅ ፋይዳ የተነሳ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጥብቅ የስነ- ህይዎት መገኛ (world Biosphere Reserve) ተብሎ የተመዘገበ መሆኑን አውስተዋል፡፡

በምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት የዘላቂ አካባቢ ጥበቃ ፕሮግራም ስራ አስኪያጅ ዶ/ር እሸቴ ደጀን ባቀረቡት የመወያያ ፅሁፍ ብሉ ኢኮኖሚ ማለት ውሃ ጋር ትስስር ያላቸው ተቋማት የሚያመነጩት ኢኮኖሚ ማለት ነው፡፡ ብሉ ኢኮኖሚ የተለያዩ ጸጋዎች አሉት ከነዚህም መካከል ከሀይድሮ ኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጨት፣ አሳዎች፣ ወደቦች፣ የባህር ትራንስፖርትና ቱሪዝም የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

በአጠቃላይ የብሉ ኢኮኖሚ አውደ ጥናት ግብ በእያንዳንዱ ሃገር ከውሃ ጋር ትስስር ያላቸው መስሪያ ቤቶች ያላቸውን አሰራር በማጥናት ለየሀገሮች ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ መፍጠር እና በተበታተነ መንገድ የተቋቋሙ መስሪያ ቤቶችን አንድ ተቋማዊ አደረጃጀት ለመፍጠር ነው ብለዋል ዶ/ር እሸቴ፡፡

በአውደ ጥናቱም (Overview of Ethiopian Blue Economy by Anene Kejela, Enhancing science & innovation Capacity For Sasteneble Blue Economy by Dr. Soobaschand, Blue Economy in IGAD Region by Dr. Eshete) ከዚህ በላይ የተጠቀሱትን ጥናታዊ ጽሁፎች አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ- ባዳዩ-BDU

💦💦💦💧💦💦💧💦💦💦

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎

Thank you for Inviting, like, share & visiting BDU page!

ለተጨማሪመረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:-https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

 

 

 

ድንግሌን መፅሐፍ ተመረቀ

*************************

[ነሐሴ 13/2014ዓ/ም፤ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ] የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሂዩማኒቲስ ፋኩልቲ ከባህል ማዕከል ጋር በመተባበር በመምህር ስንታየሁ ገብሩ ተፅፎ ለንባብ የበቃው ድንግሌን ልቦለድ መፅሀፍ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እና ታዋቂ አርቲስቶች በተገኙበት በዩኒቨርሲቲው ጥበብ አዳራሽ በድምቀት ተመርቋል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የባህል ማዕከል ዳይሬክተር ዶ/ር አስቴር ሙሉ እንደገለጹት የባህል ማዕከሉ ኪነ-ጥበብን መሳሪያ አድርጎ ዩኒቨርሲቲውንና ከዩኒቨሪሲቲው ውጭ ያለውን ማህበረሰብ ለማስተማር እየተጋ ያለ ተቋም ነው ብለዋል፡፡

ተቋሙ በስነ-ጽሁፍ፤ በቲያትር፤ በሙዚቃ፤ በሙዚየም አስተዳደር፤ ስዕልና ቅርጻቅርጽ ስራዎች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፡፡ ተማሪዎችና የአካባቢው ወጣቶች የኪነ ጥበብ ተሰጧአቸውን እንዲፈልጉና እንዲያሳድጉም እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ ዶ/ር አስቴር ተናግረዋል፡፡

ዶ/ር  አስቴር አክለውም የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ባህል ማዕከል ለኪነ ጥበብ ስራዎች እውቅና እንደሚሰጥ በመግለፅ በእለቱ እየተካሄደ ያለው በመምህር ስንታየሁ ገብሩ የተደረሰው ድንግሌን የተሰኘው መፅሐፍ ከብዙዎች አንዱ መሳያ መሆኑን በመጠቆም ደራሲውን እንኳን ደስ አለህ ብለዋል፡፡ አርቲስት ስለሺ ደምሴና ደራሲና ጋዜጠኛ ዘነበ ወላም በመጽሀፍ ምርቃ ፕሮግራሙ ላይ በመገኘታቸው ዶ/ር አስቴር ምስጋና አቅርበዋል፡፡

የምረቃ ፕሮግራሙን የከፈቱት የሂዩማኒቲስ ፋኩልቲ ዲን ተወካይ ዶ/ር የኑስ በበኩላቸው መምህር ስንታየሁ ገብሩ ድንግሌን መጽሀፍ ጽፎ በማሳተሙ ፋካልቲአችን አርአያነት ያለውና የሚያኮራ ስራ መሆኑን እውቅና ይሰጣል ብለዋል፡፡ በዚህም የተቀዛቀዘውን የልብወለድ መጽሃፍ ህትመት እንደሚያነቃቃ ያላቸውን እምነት ተናግረዋል፡፡

ጋዜጠኛ የሺ ሀሳብ አበራ የድንግሌን መጽሃፍ ይዘት ዳሰሳ በወፍ በረር ለታዳሚው ያቀረበ ሲሆን መጽሀፉ አገር በቀል እውቀትና ማንነት ላይ መሰረት አድርጎ የተጻፈና ሁሉንም የአገሪቱ ክፍሎች ያማከለ እይታን የያዘ ነው ተብለዋል፡፡

በመጽሀፍ ምረቃ ፕሮግራሙ ላይ አርቲስት ስለሺ ደምሴና ደራሲና ጋዜጠኛ ዘነበ ወላ የተገኙ ሲሆን በመጽሃፉ ላይ ያላቸውን አስተያየትና የህይወት ልምዳቸውን ለታዳሚው አካፍለዋል፡፡

 

 

 

በድንግሌን ልቦለድ መፅሐፍ ጉዞና ፍለጋን መሰረት ያደረገ ሃይማኖትን፤ እሴትን፣ ተስፋን፣ ፅናትን፣ ማንነትን እና ኢትዮጵያዊነትን አጉልቶ የሚያሳይ የስነ-ፁሁፍ ስራ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች፤ መምህራን፣ ተማሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ- ባዳዩ-BDU

💦💦💦💧💦💦💧💦💦💦

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎

Thank you for Inviting, like, share & visiting BDU page!

ለተጨማሪመረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:-https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

 

 

የግብርና እና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ በዘንዘልማ ቀበሌ የችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር አካሄደ

(ነሐሴ 10/2014ዓ.ም፤ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-BDU) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የግብርና እና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ በዘንዘልማ ቀበሌ በሞገደል ተፋሰስ አካባቢ ከ4ሺህ በላይ ሀገር በቀል የዛፍ ችግኞችን በማፍላት መምህራን እና የአካባቢውን ማህበረሰብ በማስተባበር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂዷል፡፡

በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው የችግኝ ተከላውን ያስጀመሩት የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ግብርና መምሪያ ተወካይ ኃላፊ የሆኑት አቶ ይበልያል ወንድይፍራው በንግግራቸው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አቀፍ ልማት ተፋሰስን መሰረት ያደረገ እቅድ አዘጋጅቶ የዘንዘልማ ቀበሌ የሞገደል ተፋሰስ አካባቢን ለማልማት የወሰነውን ውሳኔ  ህብረተሰቡን  እና በጎርፍ የተጎዳውን አካባቢ የሚጠቅም መሆኑን ጠቅሰው ውሳኔው ብቻውን በቂ ባለመሆኑ የአካባቢው ህብረተሰብ በኮሌጁ የሚሰሩ የልማት ስራዎችን በመጠበቅና በመንከባከብ የልማት ስራውን መደገፍ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ በ2014 በጀት ዓመት 3.7 ሚሊዮን ችግኞችን በማፍላት በተመረጡ ቦታዎች ተተክለው ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ መፅደቃቸውን ተናግረው የችግኝ ተከላ ፕሮግራሙ እና አጠቃላይ የተፋሰስ ልማት ስራው ይበልጥ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የግብርና እና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር አሳምነው ጣሰው በዘንዘልማ ቀበሌ ስር የሚገኘው የሞገደል ተፋሰስ አካባቢ ተራራማ በመሆኑ በጎርፍ የመሽርሸር እና ይበልጥ ለጉዳት የተዳረገ በመሆኑ ኮሌጁ አካባቢውን በዘላቂነት ለማልማት በማሰብ በዛሬው እለት መምህራንን እና የአካባቢውን ህብረተሰብ በማስተባበር ሀገር በቀል የዛፍ ችግኝ ተከላ ፕሮራም ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡  እንደ ዶ/ር አሳምነው ገለፃ  ኮሌጁ ካሁን በፊት በቁሳቁስ እና በመምህራን ስልጠና እየተደገፉ ያሉት የዘንዘልማ ትምህርት ቤት እና የወተት ማህበሩ የዚህ ፕሮጀክቱ አካል በመሆናቸው ይበልጥ የማጠናከር ስራን እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡  በዛሬው እለት የተጀመረው የሞገደል ተፋሰስ አካባቢ በቋሚነት ከማልማትም ባለፈ የህብረተሰቡን የአመጋገብ እና አለባበስ እንዲሁም የአካባቢን የተፈጥሮ ሐብት ጥበቃን ጨምሮ የአካባቢው ህብረተሰብ አኗኗር የሚቀይር ዘላቂ እና ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን ለመስራት ኮሌጁ ቁርጠኛ መሆኑን ዶ/ር አሳምነው ተናግረዋል፡፡

በችግኝ ተከላው ላይ የአካባቢው ማህበረሰብ እንዳሉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለዘንዘልማ ቀበሌ ልጆቻችን የሚማሩበትን ትምህርት ቤት ከመደገፍ ጀምሮ ከብቶቻችን ሲታመሙብን እያከመ በግብርናውም ዘርፍ ባለሙያዎችን አካባቢያችን ድረስ በመላክ የተግባር ስልጠናዎችን በመስጠት ዘርፈ ብዙ ጥቅም እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡  የሞገደል ተፋሰስ አካባቢ ተራራማ በመሆኑ በጎርፍ እየተሸረሸረ ገደል በመፍጠሩ ስጋት እንደነበራቸው ተናግረው አሁን ላይ ግን የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካባቢው መልሶ ለማልማት ችግኝ በመትከል እና በቋሚነት አቅዶ ለመስራት በመምጣቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡

በችግኝ ተከላው መርሃ ግብር ላይ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ግብርና መምሪያ፣ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዚዳንት ቢሮ ዳይሬክተሮች የኮሌጁ መምህራን እና የአካባቢው ማህበረሰብ ወጥቶ ከ4ሺህ በላይ የሀገር በቀል የዛፍ ችግኞችን በጎርፍ በተጎዱ ቦታዎች ላይ ተክለዋል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

Thank you for Inviting, like, share & visiting BDU page!

ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:- https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

#BDU60th_ANNIVERSARY

 

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከአሜሪካ መንግስት ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅት (USAID) ጋር የፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረመ

 

(ነሐሴ 10/2014ዓ.ም፤ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-BDU)  ስምምነቱን የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲን በመወከል የዩኒቨርሲቲዉ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዘዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ሽፈራዉ የፈረሙ ሲሆን በዩኤስኤአይድ(USAID) በኩል ጂያን ጆን ስፊርማቸዉን አኑረዋል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ም/ፕሬዘዳንት ዶ/ር ዘዉዱ እምሩ የፕሮጀክት ስምምነቱን አስመልክተዉ እንደገለጹት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ 60ኛ ዓመቱን በማክበር ላይ ያለ ታላቅ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን ከሚሰራቸዉ ዋና ዋና ተግባራት ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ በአለም አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ሀገራት ከሚገኙ አጋር አካላት ጋር የሚሰራቸዉ የፕሮጀክት ስራዎች ናቸዉ ብለዋል፡፡

በአሁኑ ሰዓት ዩኒቨርሲቲዉ 190 የሚሆኑ አጋር አካላት ጋር በጋራ በመስራት ላይ ሲሆን በአሜሪካ መንግሰት የሚደገፈዉ (USAID) ፕሮጀክት አንዱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ፕሮጀክቱ በዋናነት ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አደጋ ስጋት መከላከልና ምግብ ዋስትና ጥናት ተቋም ጋር በጋራ አንደሚሰራ የተገለፁ ሲሆን ለመጭዎቹ አምስት አመታት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አስተባባሪነት ሌሎች አስራ አንድ ዩኒቨርሲቲዎችም ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ከሰራቸዉ ፕሮጀክቶች መካከል ይህ ትልቁ እንደሆነ የገለፁት ዶ/ር ዘዉዱ ስራዉን ለማጠናቀቅ 7.7 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ወጭ የሚጠይቅ ነዉ ብለዋል፡፡

ዶ/ር ዘዉዱ አክለውም ፕሮጀክቱም ሶስት ዋና ዋና አላማዎችን ይዞ የተነሳ ሲሆን በዋናነት የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት የሰልጣኞችን ሙያዊ ክህሎት ማሳደግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ፕሮጀክቱ በመጭዎቹ 5 ዓመታት 750 ለሚደርሱ አካላት ከፍተኛ የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት በሀገሪቱ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ አስተዋፆ ማድረግ መሆኑን ዶ/ር ዘዉዱ ገልጸዋል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

Thank you for Inviting, like, share & visiting BDU page!

ለተጨማሪመረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:-https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

#BDU60th_ANNIVERSARY

 

ለዩኒቨርሲቲው የፀጥታና ደህንነት ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ

*******************************************************

(ነሐሴ 10/2014ዓ.ም፤ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-BDU) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የፀጥታና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ከዩኒቨርሲቲው የስልጠና ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር ለዩኒቨርስቲው የፀጥታና ደህንነት ሰራተኞች ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በመጡ ባለሙያዎች ለስምንት ቀናት የሚቆይ ስልጠና በዋናው ግቢ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተጀምሯል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አራጋው ብዙዓለም ስልጠናውን ሲያስጀምሩ እንደገለጹት እዚህ ለመድረስ ጉልህ ድርሻ ላበረከቱ የፀጥታና ደህንነት ኃላፊዎች እና ሰራተኞችን አመስግነው የፀጥታ ክንፉን በልዩ ሁኔታ የምንተባበረው እና ውጤት ልናመጣበት የምንችለው የዩኒቨርሲቲው የስሜት ህዋስ ነው በማለት ስልጠናው ለዩኒቨርሲቲው ራዕይ መሳካት ዋና ግብአት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ የፀጥታና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ሀብታሙ መለሰ በበኩላቸው ስልጠናው የፀጥታና ደህንነት ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ ምን ይጠበቅብናል፣ ምንስ ማድረግ ይኖርብናል የሚሉ ጭብጦችን ይይዛል፡፡ ይህን ስልጠና ለመስጠት በኮቪድ እና በጦርነቱ ምክንያት ተራዝሞ የቆየ ቢሆንም አሁን ላይ በአጭር ጊዜ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ባለሙያዎች ስልጠናውን መስጠት በመቻላቸው ሊመሰገኑ ይገባል ብለዋል፡፡  

ስልጠናውን ያስተባበሩት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የማማከር አገልግሎት ክፍል ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ዳምጤ ውዱ ስልጠናው ለፀጥታ ደህንነት ክፍል ሰራተኞች የአቅም ማጎልበቻ መሆኑንና ለስምንት ቀናት እንደሚቆይ ተናግረዋል፡፡ መነሻውም በኢትዮጵያ 19 ዩኒቨርሲቲዎች ዳሰሳዊ ጥናት ተደርጎ በዘጠኝ ርዕሶች ላይ ያተኮረ ሲሆን የጥበቃ ስራ ምንነትና የፍተሻ ስራ፣ የፈንጅና ተቀጣጣይ ነገሮችን መለየት፣ ለስራ አጋዥ የሆነውን የጦር መሳሪያ አያያዝና አጠቃቀም፣ የዩኒቨርሲቲ የፀጥታ ስጋቶችን በመለየት እንዴት መከላከል ይቻላል የሚለውን ማወቅ፣ የመረጃ አሰባሰብና አያያዝ፤ አጠቃቀም፣ መሰረታዊ የወንጀል ህግ፣ ከአንድ የጥበቃ ስራተኛ የሚፈለግ ስነ-ምግባር እንዲሁም ደንበኞችን እንዴት ማስተናገድ አለብን የሚሉትን ርዕሶች አካቷል ብለዋል፡፡

ኃላፊው አክለውም የምንሰጠው ስልጠና ከንድፈ ሀሳብ ባሻገር በተግባር የታገዘ እና የሰልጣኞችም ተሳትፎ የታከለበት በመሆኑ ስራቸውን በምን ሁኔታ መጠበቅ እና መምራት እንዳለባቸው የተሻለ አቅም በመፍጠር በተጨባጭ ተግባር ላይ ያውሉታል ተብሎ ይታሰባል ብለዋል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

Thank you for Inviting, like, share & visiting BDU page!

ለተጨማሪመረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:-https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

#BDU60th_ANNIVERSARY

 

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከጃፓኑ ቶቶሪ ዩኒቨርሲቲ ጋር የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ
*************************************************************************
(ነሐሴ 09/2014ዓ.ም፤ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-BDU) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከጃፓኑ ቶቶሪ ዩኒቨርሲቲ እና ሌሎች ተቋማት ጋር በዘላቂ የመሬት ልማት አስተዳደር ዙሪያ ክልል አቀፍ የምርምር እና መሰል ስራዎችን ለመስራት የሚያስችል የጋራ የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡
የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ፣ የአማራ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት፣ የግብርና ሚኒስቴር፣ የጃፓን አለም አቀፍ ትገብብር ኤጀንሲ ( JICA) ፣ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና የጃፓኑ ቶቶሪ ዩኒቨርሲቲ መካከል በዘላቂ የመሬት ልማት አስተዳደር ዙሪያ ክልል አቀፍ የምርምር እና ሌሎች የልማት ስራዎችን በጋራ ለመስራት ተፈራርመዋል፡፡
የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አልማዝ ጊዜዉ፣ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬዉ ተገኘ እና የአማራ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጥላ የተክለወልድ በተገኙበት በተፈረመዉ የስምምነት ሰነድ ላይ የጃፓን አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (JICA) የቀጣይ ትዉልድ ዘላቂ የመሬት ልማት አያያዝ በሚል የኢትዮጵያን በርሀማነት ለመቀነስ የሚያስችል ፕሮጀክት ስራ የስምምነቱ አካል ሁኗል፡፡
የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አልማዝ ጊዜዉ በፕሮግራሙ ላይ ባደረጉት ንግግር በሀገራችን ከሚገኙት ተራራማ ቦታዎች 60℅ የሚሆነዉ በአማራ ከልል እንደሚገኝ በመግለፅ በርካታ የክልሉ አካባቢዎች ለመሬት መሸርሸር አመች በመሆናቸዉ በዘላቂ የመሬት ልማት አሰስተዳደር (SLM) ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት አለበት ብለዋል፡፡
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ፍሬዉ ተገኘ በበኩላቸዉ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከአቻ ዩኒቨርሲቲዎችና ተቋማት ጋር ለመስራት ያደረገዉ ስምምነት እንዳስደሰታቸዉ ገልፀዉ የጃፓኑ ጀአይካ (JICA) ፕሮጀክትም አለም አቀፍና አካባቢያዊ ችግሮች ሳይበግሩት ከዩኒቨርሲቲያችን ጋር ሲሰራቸዉ የነበሩት ስራዎች የሚያስመሰግኑት ናቸዉ ብለዋል፡፡
ከስምምነቱ ጎን ለጎን የጃፓን አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (JICA) ከዚህ በፊት ያከናዎናቸዉ ዋና ዋና ተግባራት ቀርበዉ ዉይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ ጀአይካ የሰራቸዉን ዋና ዋና ተግባራት አስመልክተዉ ማብራሪያ የሰጡን ኑሯቸዉን በጃፓን ሀገር ያደረጉትና በጃፓኑ ቶቶሪ ዩኒቨርሲቲ በጀይካ ፕሮጀክት የምርምር ስራዎችን እየሰሩ ያሉት ፕሮፌሰር ንጉሴ ሐረገወይን እንዳሉት ቶቶሪ ዩኒቨርሲቲ ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲና ሌሎች ሶስት ተቋማት ጋር በመሆን ከፈረንጆች 2017 ጀምሮ ምርምሮችን ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል፡፡ የምርምሮቹ አላማም የአፈርና ዉሃ መከላትን ቀንሶ የመሬት ምርታማነትን በመጨመር የአካባቢዉን ህዝብ ተጠቃሚነት ማስፋፋት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የጀአይካ ፕሮጀክትም በተመረጡ ሶስት አካባቢዎች አባገሪማ፣ ጉደርና ድባጤ ሲሰራ የቆየ ሲሆን የድባጤዉ ፕሮጀክት በፀጥታ ችግር ሲቋረጥ ሌሎቹ ስኬታማ እንደነበሩ ፕሮፌሰር ንጉሴ አክለዉ ገልጸዋል፡፡
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዘዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ሽፈራዉ የስምምነት ፊርማዉንና የጀአይካ ፕሮጀክት ሲሰራቸዉ የነበሩስራዎችን አስመልክተዉ በሰጡት አስተያየት ስምምነቱ ሶስት መሰረታዊ ስራዎችን ለመስራት የታሰበ ነዉ ብለዋል፡፡ በቀጣይም በምርምር፣ በትምህርትና አቅም ግንባታ ስራዎችን በትብብር ለመስራት መስማማታቸዉን ተናግረዋል፡፡
የጀአይካ ፕሮጀክትን አስመልክቶ አንደተናገሩት የፕሮጀክቱ ባለቤት ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እንደነበር ገልፀዉ አሁን ፕሮጀክቱ እየተጠናቀቀ ስለሆነ በቀጣይ ሌሎች ፕሮጀክቶችን በጋራ ለመስራት ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ተወያይተናል ብለዋል፡፡
ዶ/ር ተስፋዬ አክለዉም ፕሮጀክቱ በጎርፍ መቀነስ፣ በአፈር ልማትና በማህበረሰብ ኑሮ መሻሻል ዙሪያ ሲሰራ እንደቆየ ገልፀዉ በቀጣይ እነዚህ ስራዎች ተጠናክረዉ እንዲቀጥሉ ለማድረግ የሚያስችል ውይይት ከባለ ድርሻ አካላት ጋር መወያየታቸዉን ተናግረዋል፡፡
ባሕርዳርዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU
ከዓባይጓዳጥበብሲቀዳ
Wisdom at the source of Blue Nile
Thank you for Inviting, like, share & visiting BDU page!
ለተጨማሪመረጃዎች፡-
Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official
website :- www.bdu.edu.et

Pages