Latest News

 

ለባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስቴም ማዕከል እና ለ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የስፔስ ሳይንስ ስልጠና መስጠት ተጀመረ

*********************************************************************************

 (ሀምሌ 18/2014 ዓ.ም፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-BDU) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕ ጽ/ቤት ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ማህበረሰብ እና ዋሸራ ጂኦስፔስ እና ራዳር ሳይንስ የምርምር ማዕከል ጋር በመተባበር ባሕር ዳር ከተማ ከሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ትምርት ቤቶች የተውጣጡ እና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስቴም  ማዕከል ተማሪዎችን ጨምሮ በስነ-ፈለግ ጥናት፣ እና በሳተላይት ቴክኖሎጂ ከሐምሌ 18-23/2014 ዓ.ም ለስድት ተከታታይ ቀናት የቆየ የክረምት ወቅት ስልጠና በዋናው ግቢ የቀድሞው ሴኔት አዳራሽ መስጠት ጀመረ፡፡

ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት በሳይንስ ኮሌጅ የፊዚክስ ትምህርት ክፍል ሀላፊ የሆኑት ዶ/ር ተስፋዬ ዳኜ እንዳሉት የስፔስ ሳይንስ  ስልጠና ለልጆቹ  መስጠታችን ተማሪዎች የወደፊት የትምህርት ዝንባሌያቸው ስፔስ ሳይንስ ላይ እንዲያተኩሩና ለሀገር ጠቃሚ ዜጋ ሆነው እንዲወጡ አስተዋፆው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ስልጠናውን የሚሰጡ ባለሙያዎች ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ እና ከትምህረት ክፍሉ በሙያው እውቀት ባላቸው መምህራን መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ስልጠናው ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የ60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አከባበር ጋር ተያይዞ የሚሰጥ መሆን ገልጸው ኮሌጁ በተደራጁ ላብራቶሪዎች እና የመማሪያ ክፍሎች ታግዞ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ድግሪ በስፔስ ሳይንስ እያሰለጠነ መሆኑን የትምህርት ክፍሉ ሀላፊ ገልፀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ብሩክ ተረፈ ለሰልጣኞች ስለኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ የስራ እንቅስቃሴ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎

Thank you for Inviting, like, share & visiting BDU page!

ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:- https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

#BDU60th_ANNIVERSARY

 

 

website :- www.bdu.edu.e

MoU signed between BDU and Embassy of the Kingdom of the Netherlands 

Bahir Dar University and Embassy of the Kingdom of the Netherlands have signed a memorandum of understanding to jointly work on agriculture.  

Dr. Tesfaye Shiferaw, Vice President for Research and Community Services and Mr. Meeuwes Brouwer, Agricultural Counselor, signed the agreement on behalf of Bahir Dar University and the Embassy, respectively. The agreement aims to strengthen the development of agriculture/horticulture sector particularly in Amhara region and generally in the country.

Areas of cooperation between the parties include jointly developing and conducting demand-driven capacity building training programs for students and professors as well as commercial and small scale horticulture sector development, organizing national and international seminars, conferences and workshops on topics of mutual interest, creating a collaborative linkage with universities and industries, promoting Integrated Pest Management (IPM) practices, and  providing technical support and collaboration on improving the cold chain and processing facility establishment as well as post-harvest technology.

በፕ/ር ምንዳርአለው ዘውዴ የተፃፈ “ነገ መቼ ነው? ” መጽሐፍ  ምረቃ ተካሄደ

**************************************************************

(ሀምሌ 15/2014 ዓ.ም፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-BDU) በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የባህል ማዕከል አዘጋጅነት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና መምህር በሆኑት ፕሮፌሰር ምንዳርአለው ዘውዴ “ነገ መቼ ነው?” በሚል ርዕስ የተጻፈው መጽሐፍ ምረቃ እና የፕሮፌሰሩ የህይዎት ልምድ ተሞክሯቸውን ያካፈሉበት መርሃ-ግብር የባሕር ዳር ከተማ ወጣቶች፤ በርካታ መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች እንዲሁም ተማሪዎች በተገኙበት በዩኒቨርሲቲው ፔዳ ግቢ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሂዷል፡፡

   በመጽሐፍ ምርቃት ፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሙኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዘውዱ እምሩ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የባህል ማዕከል የፅናት፣ የማይናዎጥ አቋም ተምሳሌት የሆኑትን ኩሩ ኢትዮጵያዊ ፕ/ር ምንዳርአለው ዘውዴ በአካል ተገኝተው የህይዎት ልምድና ተሞክሯቸውን እንዲያከፍሉ እና መጽሐፋቸውንም በተቋማችን እንዲመረቅ ከፍተኛ አስተዋፆ ያበረከቱ የማዕከሉ ሰራተኞች እና በዕለቱ የተገኙ ታዳሚዎችን አመስግነዋል፡፡

 ፕ/ር ምንዳርአለው በወቅቱ ምሁር ጠል የሆነው የአስተዳደር ስርአት ያደረሰባቸው እንግልትና ጫና ሳይበግራቸው ባልተለመደ መልኩ ወደ ገጠሪቷ የኢትዩጵያ ክፍል በመሄድ የግብርና ስራቸውን በመከወን ወንድሞቻቸውን አስተምረው ለሀገር የሚጠቅሙ ምሁራን እንዲሆኑ አስተዋፅኦ ከማበርከታቸውም በተጨማሪ በእለቱ ለምረቃ የበቃውን “ነገ መቼ ነው? ”መጽሐፍን ጨምሮ የስናዳር ስንክሳሮች፣ ራስን መሰለል፣ ሰውና ሰው እና አፍን ዘግቶ ፉጨት የተሰኙ የልቦለድ መፅሐፎችን ለአንባቢያን ማበርከታቸውን ተናግረዋል፡፡ እንደ ዶ/ር ዘውዱ ገለፃ የተማረ ሰው መልካም መልካሙን ብቻ ይዞ የሚጓዝ ሳይሆን አስቸጋሪ እና ፈታኝ ሁኔታዎችን ወደ መልካም አጋጣሚ እየቀየረ የሚያድግ መሆኑን በተግባር ያሳዩ ታላቅ ሀገር ወዳድ ምሁር እና የፅናት ተምሳሌት  መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡   

   በዕለቱ የተመረቀውን “ነገ መቼ ነው? ” አዲሱ መጽሐፍ አስመልክቶ ሰፋ ያለ የዳሰሳ ጥናት  በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋና የስነ-ጹሁፍ መምህር በሆኑት በዶ/ር አንተነህ አወቀ የቀረበ ሲሆን በደራሲው ከተፃፈው ሰውና ሰው መጽሐፍ ላይ የተወሰዱ ቅንጫቢ ምንባቦችን በዶ/ር ሞገስ ሚካኤል፣ በሂሩት አድማሱ እና በሰርፀ ፈቃደ ለታዳሚዎች በንባብ  ቀርቧል፡፡

 ፕሮፌሰሩ በ1983 ዓ.ም የተደረገውን የመንግስት ለውጥ ተከትሎ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርነታቸው መባረራቸውን ጨምሮ ለ27 ዓመት ያሳለፉትን የህይወት ውጣውረድ እና ተሞክሯቸውን እንዲሁም ለሀገር ሰላምና ለህዝብ አንድነትና ፍቅር ያላቸውን የማይናወጥ ወጥ አቋማቸውን አጋርተው ከታዳሚው ለቀረበላቸው ሀሳብና ጥያቄ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

   በመጨረሻም በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የባሕል ማዕከል እንዲሁም በባሕር ዳር ከተማ አድናቂዎች የተዘጋጀውን ስጦታ ከዶ/ር ዘውዱ እምሩ እና የሀገር ሽማግሌዎችን ወክለው ከተገኙት ከአባ መስፍን አድማሱ እጅ ፕሮፌሰር ምንዳርአለው ዘውዴ ተቀብለዋል፡፡     

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

Thank YOU for visiting and inviting our pages, for your likes and shares!

ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:- https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

 

የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ከክልሎች ለተውጣጡ ሰልጣኞች በፕሮጀክት አቅፎ ስልጠና እየሰጠ ነው

(ሀምሌ 15/2014 ዓ.ም፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-BDU) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከሁሉም ክልሎች ለተውጣጡ ከ15 ዓመት በታች እድሜ ያላቸው በድምሩ 30 ሰልጣኞችን በፓይለት ፕሮጀክት አቅፎ ስልጠና ሰጥቷል፡፡

በአማራ ክልል ባሕር ዳር ከተማ አንድ የወንድ እና ወልዲያ ከተማ አንድ የሴት ሰልጣኞች የፕሮጀክቱ አካል ሲሆኑ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚም ታዳጊ ወጣቶችን አቅፎ አሰልጣኝ በመመደብ ሳይንሳዊ ስልጠና በመምህራን እየሰጠ መሆኑን የስፖርት አካዳሚው ዲን ዶ/ር ዳኛቸዉ ንግሩ ተናግረዋል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ለአገራችን የእግር ኳስ እድገት እያደረገ ያለውን ጉልህ አስተዋጽኦ በመገምገም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የአካዳሚውን ከ15ዓመት በታች ተስፋ ለኢትዮጵያ ታዳጊ የእግር ኳስ ፕሮጀክት አርባ ምንጭ ከተማ ከሀምሌ 17 እስከ ነሐሴ 01/2014 ዓ.ም ድረስ በሚያካሄደው ውድድር ላይ እንዲሳተፉ እድል ተሰጥቷል ብለዋል ዶ/ር ዳኛቸዉ ንግሩ፡፡

ዶ/ር ዳኛቸዉ አክለውም የውድድሩ አላማ አቅም ያላቸው ተወዳዳሪዎችን መልምሎ ካፍ አካዳሚ በማስገባት ለ10 አመታት ስልጠናና ሁሉን አቀፍ ትምህርት በመስጠት ብሄራዊ ቡድኑን ሊተኩ የሚችሉ ታዳጊዎችን በማይነጥፍ መንገድ ማፍራት ሲሆን የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚም የዚህ እድል ተጠቃሚ በመሆኑ ለ3 ተከታታይ አመታት ስናሰለጥናቸው የቆዩትን ታዳጊ የእግር ኳስ ፕሮጀክት ሰልጣኞችን በውድድሩ እንዲሳተፉ በማድረግ ከሌሎች ፕሮጀክቶች የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ በብዛት ተመርጠው ወደ ካፍ አካዳሚ እንደሚገቡ ትልቅ እምነት አለን ብለዋል፡፡

ለሁሉም ተወዳዳሪዎች አዲስ ታኬታ፣ መለያዎችን እና ካሳቶኒዎችን ሰጥተን በድል እንዲመለሱ ዛሬ ጠዋት በክብር ሸኝተናቸዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብም ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ስፖርት አካዳሚው ጥሪዉን ያስተላለፈ ሲሆን በውድድሩ እንዲሳተፉ ላደረጉ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት እና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከልብ እናመሰግናቸዋለን ብለዋል ዶ/ር ዳኛቸዉ፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

Thank YOU for visiting and inviting our pages, for your likes and shares!

ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:- https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

 

የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ የ2014 በጀት ዓመት የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ

(ሀምሌ 14/2014 ዓ.ም፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ BDU) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ የአስተዳደር ዘርፉን የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በኮሌጁ ግቢ አካሄደ፡፡

የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር አሳምነው ጣሰው እንደገለጹት ባሳለፍነው በጀት ዓመት ብዙውን ጊዜ አገሪቱ በገጠማት የህልውና ዘመቻ ምክንያት ከመማር ማስተማሩ ውጭ በሆነ የዘመቻ ስራ ተጠምደው መቆየታቸውን ገልፀዋል፡፡

ዶ/ር አሳምነው በማስከተል ከጦርነቱ መልስ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናዎናቸውንና ኮሌጁ የዩኒቨርሲቲውን ራዕይ ለማሳካት ስራዎችን በጥራትና በፍጥነት እየተገበረ የሚገኝ ጠንካራ ተቋም መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃኑ ገድፍ በበኩላቸው መርሃ ግብሩን ላዘጋጁና ኮሌጁ እዚህ ደረጃ እንዲደርስ ጉልህ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበው ዩኒቨርሲቲው ከ5,500 በላይ የአስተዳደር ሰራተኞች ያሉትና ከመማር ማስተማሩ ጎን ለጎን በርካታ አኩሪ ተግባራትን የሚያከናውን ግዙፍ ተቋም መሆኑን ተናግረዋል፡፡ 

አቶ ብርሃኑ በማስከተል ሁሉም ሰራተኛ ጠንክሮ መስራት እንዳለበትና ለወደፊት ለሚመጡ የስራ ፉክክርና ውድድር በቅቶ ለመገኘት የትምህርት ወረቀት ወይም እውቀት ብቻ ሳይሆን በስራ ኮከብ ተሸላሚ ለመሆን ታታሪና ምስጉን ሰራተኛ ሆኖ መገኘት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

የበጀት አመቱን የእቅድ አፈፃፀም ዋና ዋና ተግባራት በዝርዝር ያቀረቡት የግቢው ማኔጅንግ ዳይሬክተር አቶ ታደሰ መኳንንት ሲሆኑ በአስተዳደር ዘርፉ ያሉት ተግባራትም ሆነ በመማር ማስተማሩ በኩል ምቹና ሳቢ የመማሪያ ክፍሎችን ማዘጋጀት እንደተቻለ፣ በግዥ በኩልም ከተለያዩ ክፍሎች ለሚጠየቁ ፍላጎቶች የግዥ ስርዓቱን በጠበቀ መልኩ መተግበራቸውን እንዲሁም ግቢው በአረንጓዴ ተሸፍኖ ውብ፣ማራኪና ፅዱ እንዲሆን በርካታ ስራዎች መከናዎናቸውን ከቀረበው ሪፖርት ለመረዳት ተችሏል፡፡ የምድረ ግቢ ውበት ከየት ወዴት እንደተቀየረ የበፊቱንና የአሁኑን በማነጻጸር አርአያነት ያለው ስራ መሰራቱን አቶ ታደሰ በሪፖርታቸው አቅርበዋል፡፡

በሪፖርቱ ላይ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችም የተለዩ ሲሆን ጎልተው የወጡት የመጠጥ ውሃ እጥረትና የመብራት መቆራረጥ መሆናቸው ተገልፆ በቀረበው ሪፖርት ላይ ተሳታፊዎች አስተያየት እንዲሰጡ ተደርጎ ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቷል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ ኮሌጁ አሁን ካለበት ደረጃ እንዲደርስ ጉልህ አስተዋፅዖ ላበረከቱ አካላት የቀድሞ የኮሌጁ ዲን የነበሩትን ዶ/ር በላይነህ አየለን ጨምሮ ስራቸውን በትጋት ለተወጡ የክፍል ኃላፊዎች፣የስራ ፈፃሚዎች፣ሹፌሮችና የቀን ሰራተኞች የእውቅናና ሽልማት ስነ ስርዓት ተካሂዷል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎

Thank you for Inviting, like, share & visiting BDU page!

ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:- https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

#BDU60th_ANNIVERSARY

 

የአረንጓዴ አሻራ ጉዟችን በብር አዳማ ሰንሰለታማ ተራሮች!

(ሀምሌ 13/2014 ዓ.ም፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ BDU) በምዕራብ ጎጃም ዞን ቋሪት፣ ይልማና ዴንሳ እና ሰከላን አዋስኖ የሚገኘው ብር አዳማ ሰንሰለታማ ተራራ ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ የተራቆተውን አካባቢ በደን የመሸፈን እና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የማድረግ ስራ ዛሬም ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው፡፡

የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሩን ያስጀመሩት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳት ዶ/ር ተስፋዬ ሽፈራው እንደተናገሩት አፈርና ውሃ ጥበቃ ከአረንጓዴ አሻራ ጋር ተያይዞ ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ የብር አዳማ ሰንሰለታማ ተራሮችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ በየአመቱ የሚተከሉትን ችግኞች ለመመልከት እና ህብረተሰቡን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ችግኞችን በመትከል ደኑን የማስፋት ስራ እየተሰራ ሲሆን ከዚህ ባሻገር ዩኒቨርሲቲው ባስገነባው ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ እየተገነባ ያለው ንፁህ የመጠጥ ውሃ በቅርቡ ተጠናቆ ለማህበረሰቡ አገልግሎት እንደሚሰጥ ገልፀዋል፡፡

ዶ/ር ተስፋዬ አያይዘውም የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማር ስራው ጎን ለጎን የህብረተሰቡን ችግር ሊፈታ የሚችል የምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎችን እንደሚያከናውን ጠቁመው የወረዳ አመራሮችም ዩኒቨርስቲው ቴክኖሎጂዎችን ሲያስተዋውቅ መሬት ላይ ወርደው እንዲተገበሩ የበኩላቸውን እንዲወጡ እና የሚተከሉ ችግኞችን ደግሞ በመንከባከብ በባለቤትነት እንዲይዙ አመራርና ማህበረሰቡን አደራ ብለዋል፡፡

በስነ-ስርዓቱ የተገኙት የቋሪት ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወርቅነህ ድረስ በበኩላቸው ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ብር አዳማ ተራራን ከጉዳት ለመታደግ እና የማህበረሰቡን ችግር ለመፍታት ከ30 በላይ አርሶ አደሮችን አዊ ዞን ድረስ በመውሰድ አሰልጥኖ ልምድ እንዲቀስሙ በማድረግ በተራቆቱ መሬቶች ዲከረንስ የተባለ ችግኝ በመትከል ለከሰል ምርት እንዲውልና ወጣቱን ተጠቃሚ በማድረግ ሰፊ ስራ መሰራቱን አስታውሰዋል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU

Description: 💦Description: 💦Description: 💦Description: 💧Description: 💦Description: 💦Description: 💧Description: 💦Description: 💦Description: 💦

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎

Thank you for visiting our page!

ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:- https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

#BDU60th_ANNIVERSARY

 

የተሻለ የፈጠራና የቢዝነስ ሃሳብ ያላቸዉ ወጣቶች ተሸለሙ
************************************************
(ሐምሌ 08/2014 ዓ.ም፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲBDU)
በባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ፣ ኢንዲያና ዩኒቨርሲቲ፣ ደ/ማርቆስ ዩኒቨርሲቲና አይቪ ቴክ ኮሚኒቲ ኮሌጅ ትብብርና በአሜሪካ ኤምባሲ የገንዘብ ድጋፍ እየተተገበረ የሚገኘዉ ፓይቤልት (Partnership in Business Entrepreneurship and leadership Transformation /PIBELT/ ፕሮጀክት በሥራ ፈጠራ ስልጠና ላይ ሲሳተፉ የነበሩ ወጣት ስራ ፈጣሪዎችን በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበብ ህንፃ አዳራሽ ባለድርሻ አካላትና ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች በተገኙበት ለስራ መጀመሪያ የሚሆን የገንዘብ ሽልማት (Seed money award) ተበረከተ፡፡
በሽልማት ፕሮግራሙ ላይ በመገኘት ስለ ፕሮጀክቱ ማብራሪያ የሰጡት የፕሮጀክቱ ኃላፊ ዶ/ር ጌታሁን የማታ ፕሮጀክቱ 3 አላማዎችን አንግቦ ይንቀሳቀሳል ብለዋል፡፡ እነዚህም፡
1ኛ.በባሕር ዳር−ደ/ማርቆስ ኮሪደር ያለዉን ኢንተርፕርነርሽፕ ስነ−ምህዳር ማጠናከር፣
2ኛ. የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አመራሮችን አቅም መገንባትና
3ኛ. ተቋማዊ ትስስር መፍጠር ዋነኞቹ ናቸዉ ብለዋል፡፡
ዶ/ር ጌታሁን አክለዉም ሽልማቱ ለሁለተኛ ጊዜ የተሰጠ መሆኑን ገልፀዉ በመጀመሪያዉ ዙር 5፣ በዚህ ዙር ደግሞ 6 የቢዝነስ ሃሳብ ላላቸው ወጣቶች እንደተሰጠና ለሁለቱ ዙር ሽልማቶች ከ800,000 ብር በላይ ወጭ ተደርጓል ብለዋል፡፡ ወጣቶቹ ሽልማቱን ከወሰዱ በኋላም ክትትል እናደርጋለን ያሉት ዶ/ር ጌታሁን ፕሮጀክቱ ቢጠናቀቅም በዩኒቨርሲቲዉ በሚገኘዉ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማትና ማበልፀጊያ ማዕከል በኩል ክትትሉ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት እና ማበለጸጊያ ማዕከል (Entrepreneurship Development and Incubation Center- EDIC) ማዕከል ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዘዉዱ ላቀ በበኩላቸዉ ማዕከሉ ከሚሰጣቸው የስራ ፈጠራና ተያያዥ የስልጠና ዘርፎች ዉስጥ የንግድ ልማት ስልጠናና ምክር፤ የስራ አመራር ስልጠናና ምክር ወ.ዘ.ተ. በተጨማሪ ከልዩ ልዩ ተቋማት ጋር በጋራ ዘላቂ የስራ ፈጠራ ምህዳር (Sustainable entrepreneurship ecosystem) ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን እንስተዋል፡፡ ማዕከሉ ልዩ ልዩ የስራ ፈጠራ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ለዩኒቨርስቲው ተማሪዎች፤ ለተመረቁ ተማሪዎች፤ ለመምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች፤ እንዱሁም ለአካባቢው ወጣቶችና የንግድ ማህበረሰብ ስልጠናና ምከር አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ አብራተዋል፡፡
ማዕከሉ የዩኒቨርሰቲውን ተደራሽነትና ራዕይ ለማሳካትም በፈጠራና አለማቀፋዊነት (Innovation and Internationalization) ረገድም ጉልህ ሚና እንዳለውና ድርሻውንም እየተወጣ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የዉጭፕሮጀክቶች ኃላፊና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ገበየሁ መንገሻፕ ሮጀክቱ ለሁለት ዓመታት የትግበራ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል፡፡
በዩኒቨርሲቲዉ እየተተገበሩ ካሉ ዉጤታማ ፕሮጀክቶች በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ አንዱ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ገበየሁ ፕሮጀክቱ ለወጣቶቹ ተከታታይ ስልጠና የሰጠ ሲሆን ለወጣቶቹ የስራ መስሪያ ቦታ እና ልዩ ልዩ ድጋፎችን እንዲያገኙ ከተለያዩ ተቋማት ጋር አብረዉ እንዲሰሩ የማስተሳሰር ስራ ዩኒቨርሲቲዉ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
በአሜሪካ ኤምባሲ የገንዘብ ድጋፍ የሚንቀሳቀሰዉ ይህ ብሮጀክት ከ20 ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ዉስጥ በዚህ ዙር ለ6ቱ ለስራ መጀመሪያ ሊሆን የሚችል 403,600 ብር የማበረታቻ ሽልማት ሰጥቷል፡፡
በሽልማት ስነ−ስርዓቱ ላይ ተገኝተዉ የማበረታቻ ሽልማቱን የሰጡት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዘዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ሽፈራዉ ለተሸላሚዎች ባስተላለፉት መልዕክት “ሽልማቱ ዘር ነዉ፤ዘር ደግሞ አይበላም” ስለሆነም ይህንን እርሾ ይዛችሁ ቢዝነሳችሁን እንዲታሳድጉ እንጅ ለዕለታዊ ፍጆታ እንዳታዉሉት ሲሉ አሳስበዋል፡፡ አዲስ አበባ የሚገኘዉን የአሜሪካ ኤምባሲ በመወከል በዕለቱ መልዕክት ያስተላለፉት አቶ ጌዲዮን ማሞ በበኩላቸዉ የአሜሪካ ኤምባሲ ከሚሰራቸዉ ስራዎች (University Partnership Initiatives-UPI) ፕሮጀክቶች ዉስጥ አንዱ የPIBELT ሲሆን ዉጤታማ ፕሮጀክት መሆኑን እንስተዉ የፕሮጀክቱን ስታፎች አመስግነዋል፡፡ እንዲሁም የስራ ፈጣሪ ወጣቶችን በማመስገን የተሰጣቸዉን የስራ መጀመሪያ ገንዘብ ለተጠቀሰዉ አላማ ማዋል እንደሚገባቸዉና ዩኒቨርሲቲዉም ዘላቂ ክትትልና ድጋፍ ሊያደርግላቸዉ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በሽልማት ስነ−ስርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአማራ ክልል ሳይንስና ቴክኖሎጅ ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር አቶ መላኩ ጥላሁን መስሪያ ቤታቸዉ ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በጋራ እንደሚሰራ ገልፀዉ በዩኒቨርሲቲና ኢንዱስትሪ ትስስር ዙሪያ በርካታ ስራዎች እንዲሰሩ እናደርጋን ብለዋል፡፡ አቶ መላኩ አክለዉም የቢዝነስ ሃሳቦቹ ፈቃድ ከሌላቸዉ ፈቃድ እንዲያገኙ እንደሚያድርጉ ለተሸላሚዎች ተናግረዋል፡፡
በእለቱ ከፋይናንስ ተቋማት የተገኙ ተጋባዥ እንግዳዎች ስራ ፈጣሪ ወጣቶች የንግድ ስራቸዉን ለማሳደግ የሚያግዙዋቸዉ ልዩ ልዩ የፋይናንስ ማዕቀፎች መኖራቸዉን የጠቆሙ ሲሆን ስራ ፈጣሪ ወጣቶችን ለመደገፍ የፕሮጀክት ፋይናንስ እና የሊዝ ማሽን ፋይናንስ እየሰጡ መሆናቸዉን ገልፀዉ ወጣቶቹ የማዕቀፎቹ ተጠቃሚ እንዲሆኑ አሳስበዋል፡፡ ከላይ ከተገለፁት የፈይናንስ ማዕቀፎች በተጨማሪ በንግድ ሀሳብ ላይ የተመሰረተ (idea financing) የፋይናንስ ማዕቀፍ ለመስጠት በሂደት ላይ መሆናቸዉን ገልፀዋል፡፡
የንግድ ሀሳቦችን በይበልጥ ለማሳደግና ከፋይናንስና የቦታ አቅርቦት በተጨማሪ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ልዩ ልዩ የክህሎት ስልጠና፤ የንድግድ ልማት አገልግሎቶች እና የምክር አገልግሎት በዩኒቨርሲቲዉ የስራ ፈጠራ ማዕከልና በአጋር አካላት ትብብር ቀጣይነት ባለዉ መልኩ እንዲመቻችላቸዉ አሳስበዋል፡፡
በሽልማት ስነ−ስርዓቱም መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ግብረ ሰናይ ድርጅት ተወካዮች፣የልማት ባንክና አዋሽ ባንክ ተወካዮች፣የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች በመገኘት ለስራ ፈጣሪዎች ያላቸዉን አጋርነት አሳይተዋል፡፡

According to Fantahun Ayele, when the training commenced in September 1963, there were 10 Ethiopian and 14 Russian instructors to teach major area courses. In addition, 12 Ethiopian and 2 Indian teachers were  employed to offer general academic subjects like Amharic, English, Mathematics, Physics and History.

Pages