Latest News

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመረብ ኳስ የጤና ቡድን ተጋጣሚውን በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆነ

===================================================================

(ሰኔ23/2014 ዓ/ም ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ) የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ከባሕር ዳር ከተማ ቮሊቦል ፌደሬሽን ጋር በጋራ በመሆን ከመጋቢት 17/2014 ዓ.ም እስከ ሰኔ 23/2014 ዓ.ም በ12 መስሪያ ቤቶች መካከል ሲካሄድ የቆየው የጤና ስፖርት የቮሊቦል ውድድር በዛሬው እለት ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመረብ ኳስ ጤና ቡድን ከቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (ፖሊ ግቢ) የመረብ ኳስ የጤና ቡድ ለፍፃሜ ያገናኘ ሲሆን ዛሬ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ላይ በሚኒሊየም የስፖርት ሜዳ ባደረጉት ጨዋታ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመረብ ኳስ የጤና ቡድን 3ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የዋንጫና የወርቅ መዳሊያ ባለቤት ሆኗል።

ሁለቱ ተጋጣሚ ቡድኖች ባደረጉት የፍፃሜ ጨዋታ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመረብ ኳስ የጤና ቡድን በተጋጣሚ ቡድኑ ላይ ፍፁም የበላይነት በመያዝ ነው ያሸነፈው፡፡ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ከባሕር ዳር ከተማ ቮሊቦል ፌደሬሽን ጋር በጋራ በመሆን ባዘጋጀው ውድድር ላይ የውድድሩ ኮከብ አሰልጣኝ ዶ/ር ዘመኑ ተሾመ እና የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች ደረሰ ዳኛው ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመረብ ኳስ የጤና ቡድን አሸናፊ በመሆናቸው ከባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ስፖርት መምሪያ ቡድን መሪ ከአቶ ፍቃዱ ማሞ እና ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ዲን ከዶ/ር ዳኛቸው ንግሩ እጅ የምስክር ወረቀት እና የዋንጫ ሽልማቱን ተቀብለዋል፡፡

 

የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ያገኙ 5 መምህራን እና ተመራማሪዎች የህይወት ልምዳቸውን አካፈሉ

************************************************************************

(ሰኔ 17/2014 ዓ/ም፤ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በያዝነው ዓመት  የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ እድገት የተቀበሉ አምስት አንጋፋ ምሁራን የህይወት ልምዳቸውን ያካፈሉበት መርሃ-ግብር የዩኒቨርሲቲውን ፕሬዚዳንት ጨምሮ በርካታ መምህራን፣ የአስተዳደር ሰራተኞች እና ተማሪዎች በተገኙበት ሰኔ 17/2014 ዓ.ም በቀድሞው ሴነት አዳራሽ ተካሂዷል፡፡

መርሃ-ግብሩ በኦሮሚያ ክልል ምእራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ በቶሌ ቀበሌ የተጨፈጨፉ ንፁኋን የአማራ ተወላጆችን በማሰብ የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማድረግ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ በተገኙበት ተጀምሯል፡፡ ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ እድገት የተሰጣቸው አንጋፋ መምህራን እና ተመራማሪዎችን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ዶ/ር ፍሬው አክለውም በፕሮፌሰርነት ማዕረግ ማደግ በብዙ መልኩ የዩኒቨርሲቲውም እድገት እንደሆነ ተናግረው፤ የፕሮፌሰር ማዕረግ እድገት  ስትደርሱ  ስራ የምትጀምሩበት ወቅት እንጅ ጡረታ የምትወጡበት ጊዜ ባለመሆኑ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እንደ  አንድ የምርምር ዩኒቨርሲቲ የበሰሉ እና ጠንካራ ጥናቶችን ከመስራትም ባለፈ ያገኛችሁትን እድገት ተጠቅማችሁ የበለጠ ወደ ማህበረሰቡ እንድትቀርቡና የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ የመፍትሄ ሀሳቦችን ከማመንጨት አንፃር ዩኒቨርሲቲው ከእናንተ ብዙ ይጠብቃል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በመርሃ-ግብሩ እንደተገለፀው በቆዳ ህክምና (Dermatovenerology) ፕሮፌሰር ወንድማገኝ እምቢያለ ከህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ በ Organic Chemistry ፕሮፌሰር አታክልት አበበ ከሳይንስ ኮሌጅ፣ በ Algebra ፕሮፌሰር ብርሃኑ አሳዬ ከሳይንስ ኮሌጅ፣ በሥርዓተ- ትምህርት እና መመሪያ (curriculum and instruction) ፕሮፌሰር ሰለሞን መለሰ  ከትምህርትና ስነ-ባህሪ ሳይንስ ኮሌጅ እና በአካባቢ እና የተፈጥሮ ሀብት አስተዳደር (Environment and Natural Resource management) ፕሮፌሰር አማረ ሰውነት ከማሕበራዊ ሳይንስ ፋኩልቲ የሙሉ ፕሮፈሰርነት ማዕረግ በማግኘታቸው የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ  የሙያ ዘርፎች የፕሮፌሰሮችን ቁጥር ከ20 በላይ ማድረሱን ተከትሎ ወደፊት ጠንካራ የምርምር ዩኒቨርሲቲ ሆኖ ለመቀጠል አስተዋፆው የጎላ መሆኑ ተገልጿል።  

እድገቱን ያገኙ ፕሮፌሰሮችም ለመርሃ-ግብሩ ተሳታፊዎች የህይወት ተሞክሮ እና  ልምዳቸውን እንዲሁም በቆይታቸው ያሳተሟቸውን የምርምር ጽሁፎችን እና በወቅቱ ያጋጠሟቸውን ተግዳሮቶች በዶ/ር ማረው አለሙ መድረክ መሪነት አቅርበዋል፡፡ በቀረበው የህይወት ተሞክሮ እና  ልምድ ላይ ተሳታፊዎች ጥያቄዎችን እና አስተያየቶችን አንስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ 

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU

Description: 💦Description: 💦Description: 💦Description: 💧Description: 💦Description: 💦Description: 💧Description: 💦Description: 💦Description: 💦

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎Description: 🔎

Thank YOU for visiting and inviting our pages, for your likes and shares!

ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:- https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

 

የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በውስጥ ጥራት ኦዲት ላይ ውይይት አካሄደ

**************************************************************

(ሰኔ 17/2014ዓ.ም፣ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ባዳዩ) የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከJhpiego Ethiopia ጋር በመተባበር የውስጥ ጥራት ኦዲት ላይ የኮሌጁ አመራሮች እና ሌሎች ተሳታፊዎች በተገኙበት Comprehensive nursing, Pharmacy,Medicine, Midwifery, Pediatrics, Emergency and Critical Care Nursing, Anesthesia, Medical Laboratory የሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም የሚሰጡ የትምህርት ክፍሎች የጥናት ፅሁፋቸውን በማቅረብ በጥበብ አዳራሽ የሁለት ቀን ውይይት አካሄዱ፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጥራት ቁጥጥር እና ተቋማዊ ለውጥ ዳይሬክተር ዶ/ር ነብዩ ሺታዬ እንደገለጹት ኮሌጁ የውስጥ ጥራት ኦዲትን ለሁለተኛ ጊዜ ያካሄደ ሲሆን ዋና ዓላማው መድረስ የምንፈልግበት እና አሁን ያለንበት ክፍተትን በመለየት፣ የጎደለውን በመሙላት ማሻሻል እና እውቅና መስጠት ሲሆን በዚህም እራሳችን ለራሳችን የውስጥ ጥራት ኦዲት ማድረጋችን ሌሎች አቻ ተቋማትን ለመወዳደር ያስችላል ብለዋል፡፡

ዳይሬክተሩ አክለውም አንድ ተቋም በየጊዜው የውስጥ ጥራት ኦዲት የማያደርግ ከሆነ ጉድለቱን አያውቀውም በተጨማሪም በሌሎች ድርጅቶችም ድጋፍ ለማድረግ እንዳይችሉ ምክንያት እንደሚሆን ገልፀዋል፡፡

 

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ- ባዳዩ-BDU

💦💦💦💧💦💦💧💦💦💦

ከዓባይጓዳጥበብሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎🔎

Thank you for Inviting, like, share & visiting BDU page!

ለተጨማሪመረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:-https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

 

Ethiopian textile and fashion technology institute agrees to work with a company called Dolmel.

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በባሕር ዳር ከተማ  ዋና የገበያ ማዕከል የሚገኘውን ክፍት ቦታ ማስዋብ  ጀመረ

****************************************************************************

(ሰኔ 14/2014 ዓ.ም፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ባዳዩ) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ጋር በመሆን በዋናው የገበያ ማዕከል የሚገኘውን ክፍት ቦታ በአረንጓዴ ልማት የማስዋብ ስራ መጀመሩን ገለፀ፡፡

ዩኒቨርሲቲው የከተማውን ህዝብ ተጠቃሚ የሚያደርግ የአረንጓዴ ልማት ስራ በከተማው ውስጥ የሚገኘውን የዋናውን የገበያ ማዕከል የማስዋብና ከዚህ ጋር ተያይዞ  በቀጣይ የሚሰሩ የመኪና ማቆሚያ ፓርኪንግ፣ ለሕዝብ መገልገያ የሚሆኑ መፀዳጃ ቤቶችን እና የውሃ ተፋሰሶችን ለመገንባት ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ የምድረ ግቢ ውበት ዳይሬክተር  ዶ/ር  ደሴ አሰፋ ተናግረዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው በሚሰራው ስራ ላይ የዲዛይን ስራ፣ የማማከር፣ የማቴሪያል እና የሰው ሃይል እገዛዎችን እያደረገ ሲሆን በዛሬው እለት የተጀመረው ቦታውን በአረንጓዴ የማልማት  ስራውን እሰከ ጥቅምት 2015 ዓ.ም ድረስ በማጠናቀቅ ለከተማ አስተዳደሩ እንደሚያስረክብ ዳይሬክተሩ የተናገሩ ሲሆን በቦታው ላይ የሚሰሩ ቀሪ የግንባታ ስራዎች ከከተማ  አስተዳደሩ ጋር በመሆን የሚተገበር መሆኑም ተገልጿል፡፡

BDU Law School Ranked 1st in Memorial (Written Litigation) and 2nd in Oral Litigation in the African International Humanitarian Law Moot Court Competition

Bahir Dar University School of Law Moot court competition team ranked first in Memorial (Written Litigation) and 2nd in Oral litigation on the 2022 African Humanitarian Law Moot Court Competition organized by Firdaus Integrated Services LTD in partnership with Adekunle Ajasin University Faculty of Law and Kwara State University Faculty of Law Held in Nigeria.  Moreover, BDU Law school students' Memorial was selected as the best Memorial of all. 

The moot court team comprises of student Lidya Dessalegn and Hawi Woyo, and Yabsra Alemneh (Coach and Instructor).

Our students argued a hypothetical case before International Humanitarian Law Experts after they had submitted their Memorial and qualified for oral round. They came over competition of Preliminary Round, Quarter Final Round and Semi-finals Round to reach to the Final Round. The Dean Office of the School would like to say congratulations to Bahir dar University community, particularly the community at Law school. Mr Tegegne Zergaw, Dean of the School of Law, BDU expressed his gratitude, on behalf of the school, to the coordinator, the Team members and the Coach for the success achieved. 

አዲሱ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ የስራ ጉብኝትና መደበኛ ስብሰባ በማድረግ ስራውን ጀመረ

*************************************************************************************

(ሰኔ 11/2014 ዓ/ም፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ) አዲሱ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ የስራ ጉብኝትና መደበኛ ስብሰባውን በማድረግ ሰኔ  11/2014 ዓ.ም ስራ ጀመረ፡፡

ስራ አመራር ቦርዱ ስራ በጀመረበት በዚሁ ቀን ዩኒቨርሲቲው በመማር ማስተማር ፣  በምርምር እና በማህበረሰብ አገልግሎት  እስካሁን የሄደባቸው ርቀቶች  እና ያስመዘገባቸውን  ውጤቶች  አስመልክቶ የስራ ጉብኝቱን የባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ተቋም የቢዝነስ ኢንኩቤሽንና ቴክኖሎጂ ኢንተርፕረነርሺፕ ማዕከልን ተጠቅመው በሀገር ዓቀፍ ደረጃ  ተወዳድረው ተሸላሚ የሆኑ እና በተማሪዎች የተሰሩ የቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራዎችን ፣ የስቴም ማዕከልን፣ እና የጃን ሞስኮቭ ቤተ መጽሀፍትን ፣ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ተቋም  የስራ እንቅስቃሴን ፣ በፔዳ ግቢ የተገነባውን ስፖርት አካዳሚ፣ የማሪታይም አካዳሚ ወርክሾፕ እና በጥበበ ግዮን ሪፈራል ሆስፒታል የተገነባውን ግዙፍ የሪሰርች ማዕክል እና የኦክስጅን ማምረቻ  እና ኮሌጁ የሰራቸውን  ሌሎችንም  አመርቂ ስራዎችን  እና በ (ICT) ዳይሬክቶሬት ክፍል የበለፀጉ እና  ኢ-ዩኒቨርሲቲ ለማድረግ የተሰሩ እንደተማሪዎች የመረጃ አስተዳደር ስርዓት (SIMS)፣  የንብረት ግዥ አስተዳደር ስርዓት (PMS)፣  የተቋሙ የኢንፎርሜሽንና ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) ክፍል እያከናወናቸው ያሉ  በኦንላይን ለመማር የሚያስችሉ አሰራሮችን (e-learning) ን በመተግበር  የተከናወኑ ስራዎችን  ቦርዱ ምልከታ አድርጓል፡፡

በተጨማሪም አዲሱ የስራ አመራር ቦርድ የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲን የውሃ እጥረትን ለማቃለል ከከተማው ወጣ ብሎ በሰባታሚት ከተማ የተቆፈረውን የውሃ ጉድጓድ ጎብኝተው ለስራው መሳካት ከፍተኛ አስተዋፆ ላበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ አቅራቢነት ከቦርዱ ሰብሳቢ ከአቶ አዳም ፋራህ እጅ የምስክር ወረቀት ተቀብለዋል፡፡  

ይህንን ተከትሎ  ቦርዱ ከሰዓት በኋላ ባደረገው ውይይት ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ የዩኒቨሪሲቲውን  የስራ  ክንውን አስመልክቶ  ለአዲሱ የሥራ አመራር ቦርድ ማብራሪና ገለፃ አድርገዋል፡፡  የአዲሱ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አደም ፋራህ  ዩኒቨርሲቲው በምርምር በቴክኖሎጂ ስራ  ፈጠራ እና በጤናው መስክ እየሰራው ባለው ስራ መደሰታቸውን ገልፀው ዩኒቨርሲቲው  የምርምር ዩኒቨርሲቲ እንደመሆኑ ወደፊት  ለሚሰሩ ስራዎች የጋራ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ መሰራት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡  በጉብኝቱ ወቅት የተመለከቷቸውን የዩኒቨርሲቲውን ጠቅላላ የስራ እንቅስቃሴዎች አስመልክቶ ከቦርዱ አባላት ለቀረቡ ጥያቄዎች የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንትን ጨምሮ ም/ፕሬዚዳንቶች  ማብራሪያ እና ገለፃ አድርገዋል፡፡ ቦርዱ የዩኒቨርሲቲውን የ2014 ዓ.ም የሁለተኛውን ግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት  ገምግሟል፡፡ የስራ አመራር ቦርዱ በክቡር አቶ አደም ፋራህ የሚመራ ሲሆን ሌሎች የቦርድ አባላትም ተገኝተዋል።

የእንቦጭ አረምን ለመከላከል የደንገል ችግኝ መትከል ዘላቂ መፍትሄ መሆኑ ተገለፀ

****************************************************************************

[ሰኔ11/2014ዓ/ም፤ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ] የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ጽ/ቤት በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምዕራብ ደንቢያ ወረዳ ሻጎመንጌ ቀበሌ የእንቦጭ አረምን በዘላቂነት ለመከላከል የሚያስችል የደንገል ችግኝ ተከላ አካሄደ፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከአሁን በፊት በፔዳ ግቢ፤ በአባይ ወንዝ ዳር፣ በባሕር ዳር ከተማ ድብ አንበሳ ሆቴል ፊት ለፊት እና ሚካኤል አባገሪማ ቤተክርስቲያን አካባቢዎች የደንገል ችግኞችን በመትከል የአካባቢውን ስነ-ምህዳር ከመጠበቅ ባሻገር የእንቦጭ አረምን በዘላቂነት መከላከል የሚያስችሉ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱ ተገልጿል፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የደንገል ፕሮጀክት አስተባባሪ ዶ/ር ንብረት አስራደ እንደገለጹት በሻጎመንጌ ቀበሌ የተጀመረው እንቦጭን በመከላከል ወደ ጣና የሚገባውን ደለል በማስቀረት እንቦጩ ከውሃው አልፎ ወደ እርሻ ማሳው እንዳይስፋፋ ለማድረግ የደንገል ተክሉ ሚናው የጎላ ነው፡፡  ይህ ማለት ደግሞ ውሃው አካባቢ የሚኖሩ የአሳ ዝርያዎችን ጨምሮ እንስሳትም ሆነ ተክሎች ስለማይጠፉ የደንገል ችግኝ ተከላው ብዝሀ-ህይወትን ለመጠበቅ ተመራጭ መፍትሄ ነው ብለዋል፡፡

ዶ/ር ንብረት አያይዘውም በአንድ ወቅት የሰሙት የጓደኛቸውን አባባል ተውሰው‹‹ ጣና ያለ ደንገል ሰው ያለ ኩላሊት አይኖርም›› በማለት ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በየአመቱ 98 ሺህ ብር እንቦጭን ለመከላከል ቢመድብልንም ከቦታው እርቀት አንጻር ለክትትል እና የደንገል ችግኝ ለማጓጓዝ የትራንስፖርት ችግርን እንደተግዳሮት አንስተዋል፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ነፃነት በየሮ በበኩላቸው ከዚህ በፊት እንቦጭን ለመከላከል በሰው ሃይል እና በማሽን የተሞከረ ቢሆንም አሁን ላይ የደንገል ተክል እንደ ዘላቂ አማራጭና መፍትሄ ተወስዷል፡፡ በዚህም ያጋጠመን ችግር በሚተከልባቸው አካባቢዎች የሚኖረው ህብረተሰብ ግንዛቤ አናሳ መሆን እና የስራ መሳሪያዎች እጥረት መኖሩን ገልፀዋል፡፡

በሻጎመንጌ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶአደር አማረ ማንዴ ከአመታት በፊት እኔን ጨምሮ የአካባቢው ህብረተሰብ ከሐይቁ አሳ በማስገር ተጠቃሚ ነበረ፡፡ በአሁኑ ጊዜ ግን እንቦጭ እንዲስፋፋ ያደረገው አንዱ ደለል ወደ ሀይቁ መግባት ስለሆነ በደንገል ተክል ደለሉን በመያዝ አካባቢው ያጣውን የአሳ እርባታ ለመመለስ የሚደረገው ሙከራ መልካም ነው ብለዋል፡፡

 

 

የ‘ሶሳይቲ ፎር ኢኮቱሪዝም ኤንድ ባዮዳይቨርሲቲ ኮንሰርቬሽን በጎ አድራጎት ማኅበር የለሙ ቦታዎችንና የተተከሉ ችግኞችን በተለያየ የስራ ኃላፊነት ላይ ባሉ አመራሮች አስጎበኙ

ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የተመሰረተው የ‘ሶሳይቲ ፎር ኢኮቱሪዝም ኤንድ ባዮዳይቨርሲቲ ኮንሰርቬሽን በጎ አድራጎት ማኅበር በቤዛዊት ተራራ ዙሪያ የለሙ ቦታዎችንና የተተከሉ ችግኞችን በዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ከከተማ አስተዳደሩ በመጡ የተለያዩ የስራ ኃላፊዎች በ10/10/14 ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የሶሳይቲ ፎር ኢኮቱሪዝም ኤንድ ባዮዳይቨርሲቲ ኮንሰርቬሽን ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ትዝታ የኔዓለም ማኅበሩ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከ4 ሺህ በላይ አባላት እንዳሉት ገልፀው ማህበሩ የቤዛዊት ተራራን ለማልማት አቅዶ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ስራ አስኪያጇ አክለውም ተራራው በአገር በቀል ችግኝ ለማልማት በርካታ ችግኞች በችግኝ ጣቢያቸው እንዳሉና በቅድሚያ በመጤ አረም (ላንታና) የተወረረውን የማፅዳት ስራ በሰፊው መከናወኑን አስገንዝበዋል፡፡

ሁሉም አመራር የተራራውን ሰፊ ቦታ ተዘዋውሮ ሲጎበኝ ከአሁን በፊት ተራራውን ለማልማት እንቅፋት የሆነውን መጤ አረም (ላንታና) ሙሉ በሙሉ ከተራራው ለማጥፋትና በጎርፍ ተጠርጎ የሚወሰደውን ለም አፈር ለማስቀረት ብሎም ውሃን አቁሮ ለማቆየት የሚያስችል የእርከን ስራ መሰራቱን ጉብኝቱን የመሩት አቶ ጌታነህ ምንይችል ተናግረዋል ፡፡

ከጉብኝቱ መልስ ሰፊ ውይይት ሲካሄድ ውይይቱን የመሩት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ሽፈረው፣የአ.መ.ል.ድ. ም/ስራ አስኪያጅና የማህበሩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ደጀኔ ምንልኩ፣ የባሕር ዳር ከተማ የከቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ አስራት ሙጨ፣ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ግብርናና  መሬት  መምሪያ  ኃላፊ  አቶ ትልቅሰው  እንባቆም እና ከአካባቢጥበቃ ባለስልጣን አቶ በልስቲ ፈጠነ ሲሆኑ በተደረገው ጉብኝት የታየውና ተራራውን ለማልማት በቅድሚያ መጤ አረሙን (ላንታናን) የማስወገድ ስራ በሰፊው መሰራቱ ይበል የሚያሰኝ ተግባር መሆኑ ተገልጿል፡፡

አቶ ደጀኔ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለማህበሩ ለሚያደርገውን ያላሰለሰ ድጋፍና ክትትል ምስጋና አቅርበው ሌሌችም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተራራውን ለማልማት ተቀናጅቶ በመስራት ከፅንሰ ሃሳብ የዘለለ ተግባር ተኮር ስራ ማከናወንና ተራራውን ከስጋት ቀጠና አላቆ የቱሪስት መስብ ማድረግ ተገቢ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አቶ ደጀኔ አክለውም ቦታው ትኩረት የሚሻው መሆኑን አስገንዝበው እንደዚህ ስናስታውሰው ብቻ ሳይሆን ሁሉም የሚመለከተው አካል ድርሻውን በመወጣት መጠነ ሰፊ ስራ ተሰርቶ ተራራው ደረጃውን የጠበቀ የቱሪስት መዳረሻ ሆኖ ማየት እንደሚሹ ገልፀዋል፡፡

ዶ/ር ተስፋዬ በበኩላቸው የአካባቢው ማህበረሰብ ያለምንም ስጋት የሚንቀሳቀስበት፣ የሚዝናነበትና ለከተማውም የገቢ ማስገኛ ሆኖ ቱሪስቶችን የሚስብ ስራ ለመስራት ሁሉም መረባረብ ስላለበት ከዩኒቨርሲቲ ውጭ ያሉ ተቋማትም በምርምር የተደገፈ ስራ በተራራው ላይ ሰርተው ጥሩ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡

ወ/ሮ አስራት ማህበሩ ተራራውን ለማልማት ስላደረገው አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበው ጉዳዩን የሁላችን አድርገን በመውሰድ ከማን ምን ይጠበቃል የሚለው ተለይቶ እንዲታወቅና ለወደፊት ሁሉም ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ አስገንዝበዋል፡፡ በተጨማሪም በአሁኑ ወቅት የአማራ ልዩ ኃይል ቤተመንግስቱን እንዲጠቀምበት ስለተደረገ በአካባቢው የነበረው ስጋት መወገዱን ጠቁመው ለማህበረሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እንዲሰራና ሁሉም ተረባርቦ ተራራው በማልማት የከተማውን ውበት መጨመር እንደሚቻል ወ/ሮ አስራት ተናግረዋል፡፡

የጉብኝቱ ተሳታፊዎች የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች፣ጉዳዩ የሚመለከታቸው የከተማው ሴክተር መስሪያ ቤት ኃላፊዎችና የማህበሩ አባላት ሲሆኑ በተካሄደው ሰፊ ጉብኝትና ውይይት ማህበሩ የወደፊት የትኩረት አቅጣጫውን እንዲለይ መደረጉንና በቅርቡ በርካታ ችግኞች እንደሚተከሉ ተገልጿል፡፡

በሙሉጎጃም አንዱዓለም

 

የአሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠነው

የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ የስልጠና ዳይሬክቶሬት ከዩኒቨርሲቲው ኤች/አይ/ቪ/ኤ/መከ/መቆ ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር ቅድመ ትምህርት ከHIV ጋር ያለው ግንኙነት ላይ መሰረት ያደረገ ስልጠና ከሰኔ 9 እስከ 10/2014 ዓ.ምድረስ እየሰጠ ነው፡፡

የአሰልጣኞች ስልጠናው ከህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ ከትምህርትና ስነ-ባህሪ ኮሌጅ እና ከኤች/አይ/ቪ/ኤ/መከ/መቆ ዳይሬክቶሬት ለተውጣጡ 25 መምህራን ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ የስልጠና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ወርቁ አበበ ገልፀዋል፡፡

ስልጠናውን ሲሰጡ ያገኘናቸው የህብረተሰብ ጤና ስፔሻሊስት የሆኑት አቶ ምክሩ ሽፈራው እንደተናገሩት ቅድመ ትምህርት ከHIV ጋር ያለው ግንኙነት ምን ይመስላል እንዲሁም የአቻ ግፊትን እንዴት መከላከል ይቻላል፣ ከHIV አንፃር አገራችን ያለችበት ሁኔታ ምን ይመስላል የሚለውን በመወያየት መከላከያ መንገዶችን የተመለከቱ ሀሳቦች ላይ ስልጠናው ትኩረት እንደሚያደርግ አመላክተዋል፡፡

Pages