Latest News

በሎጂስቲክስና አቅርቦት ሰንሰለት አስተዳደር ስራዎች ትግበራ ላይ ውይይት ተካሄደ

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በሎጂስቲክስና አቅርቦት ሰንሰለት አስተዳደር ስራዎች አተገባበር ላይ ትኩረቱን ያደረገ ውይይት አካሂዷል፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የሎጂስቲክስና አቅርቦት ሰንሰለት አስተዳደር ትምህርት ክፍል ኃላፊ ኃይሉ አበበ እንደገለጹት የዛሬው ውይይት ከአንድ አመት በፊት ዩኒቨርሲቲው ከKHUNE ፋውንዴሽን ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሞ እንደነበር አስታውሰው የሰነዱ ዋና ጭብጥ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ላይ በሎጂስቲክስና አቅርቦት ሰንሰለት አስተዳደር ዘርፍ ክፍተት በመኖሩ ጥህን ለመቅረፍ የትምህርት ፕሮግራሞች ሊከፈቱ ይገባል የሚል ነበር፡፡ በስምምነት ሰነዱ በጋራ ለመስራት ከተስማማንባቸው ሰባት ዋና ዋና ዘርፎች ውስጥ ምን ያክሉ ወደ ተግባር ገብተዋል ምን ምን ስራዎችስ በስምምነቱ መሰረት ተከናውነዋል የሚለው ቀርቦ ውይይት የተደረገበት መሆኑን አቶ ኃይሉ አበበ ተናግረዋል፡፡

ባለፍው አመት ግንቦት ወር ላይ KHUNE ፋውንዴሽን ሙሉ ወጭውን ሸፍኖ በተዘጋጀው መድረክ በርካታ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት የተደርገ ሲሆን መንግስትም የፖሊሲ ሰነድ አቅርቦ ውይይት ተደርጎበት፤ በሰነዶች ላይ ግብአት የተሰበሰበበትና ምሁራንም አስተያየት የሰጡበት መድረክ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

አክለውም በርካታ የምርምር ስራዎችንም በጋራ በመስራት ላይ እንደሚገኙና በማህበረሰብ አገልግሎትም ፕሮጀክቶች ተቀርጸው ወደ ስራ እንደተገባ ገልፀዋል፡፡ KHUNE ፋውንዴሽን አቅም መገንባት አንዱ የውስጥ እቅዱ ስለሆነ የሦስተኛ ዲግሪ በሎጂስቲክስና አቅርቦት ሰንሰለት አስተዳደር ትምህርት በዚህ አመት እንዲጀመር የስርአተ ትምህርት ቀረጻ እና በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም ላይ ተማሪዎቻችን የስራ ልምምድ በሚወጡበት ጊዜ ሙሉ ትኩረታቸውን ልምምዱ ላይ እንዲያደርጉ ወጫቸውን መሸፈን ላይም ድጋፍ አድርጓል ብለዋል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምር ዩኒቨርሲቲ እንደመሆኑና በአፍሪካም እራሴን ግንባር ቀደም አደርጋለሁ ብሎ ባስቀመጠው ራዕይ ልክ እየተንቀሳቀሰ ስለመሆኑ ከውጭ አጋር አካላት ጋር የሚያደርጋቸው የስራ ስምምነቶች ማሳያዎች ናቸው ብለዋል ምሁሩ ፡፡

ዩኒቨርሲቲው ተምረው የሚወጡ ተማሪዎች አለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ማድረግ የሚያስችሉ ፕሮግራሞችን እየቀረጸ በማስተማር ላይ መሆኑን ያሳየበት ሲሆን ይህም  የከፍተኛ አመራሩን ቁርጠኝነትና ድጋፍ የሚያሳይ ነው ብለዋል አቶ ኃይሉ አበበ፡፡

የውይይቱ ተሳታፊዎችም ባልተቀላጠፈ የሎጀስቲክስ ስርዓት ኢኮኖሚያዊ እድገትን ማረጋገጥ አይቻልም፤ የግብርና ዘርፉ ግብዓቶች፣ የፋብሪካ ማምረቻ ጥሬ እቃዎች እና የጤና ተቋማት የህክምና መገልገያ መሳሪያዎችን እና መድሃኒት ማምረትና ማከፋፈል፣ እንዲሁም አጠቃላይ የንግድ ስርዓቱ ያለ ሎጀስቲክስ እንደማይታሰብ ተናግረዋል፡፡

 

በውይይቱ ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ እና ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፤ የኤልያስ መልአክ ፋውንዴሽን የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ኤሊያስ መላክ እና የKHUNE ፋውንዴሽን የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

 

 

በዝቅተኛ የስራ መደብ ላይ ለሚገኙ ሰራተኞች ደረጃ ለማሻሻል እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

***************************************************************

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በዝቅተኛ የስራ መደብ ላይ ለሚገኙ ሰራተኞች እውቀት፤ ክህሎትና ደረጃ ማሻሻል የሚያስችል ስራ እየስራ መሆኑን ገለጸ፡፡

የባሕር ዳር  ዩኒቨርሲቲ  የአስተዳደር  ጉዳዮች  ም/ፕሬዚዳንት  አቶ  ብርሃኑ  ገድፍ  እንደገለጹት በዩኒቨርሲቲዎች ምግብ ቤት የሚሰሩ ሰራተኞች በብዛት ማንበብና መጻፍ የማይችሉና በትምህርታቸው ብዙም ያልገፉ፣ ከ8ኛ ክፍል ያልዘለሉ በመሆናቸው የሰራተኞችን ደረጃ ለማሻሻል ተግዳሮት በመሆኑ ስልጠና አግኝተው COC መፈተን ነበረባቸው፡፡ ዩኒቨርሲቲው ለስልጠናው የሚያስፈልገውን ክፍያ በመክፈል እንዲሰለጥኑ አድርጓል፡፡ በመቀጠልም ለCOC ምዘና የሚያስፈልገውን ክፍያ በመክፈል እንዲመዘኑ ተደርጓል ብለዋል፡፡

ስልጠናውን ለመውሰድ 467 ሰራተኞች የተመዘገቡ ሲሆን 8ቱ በተለያየ ምክንያት ስልጠናውን አላጠናቀቁም፡፡ 459 ሰራተኞች ስልጠናውን ጨርሰው አብዛኞቹ COCውን በብቃት አልፈዋል፡፡ ይህ የሚያመለክተው ሰራተኞች ጥሩ እውቀትና ክህሎት ያላቸው መሆኑን ነው፡፡ የምግብ ቤት ሰራተኞች በተለይም እናቶች ሁልጊዜም ለዩኒቨርሲቲው የኩራት ምንጭ በመሆናቸው ዩኒቨርሲቲው ኩራት ይሰማዋል፡፡ በሌሎች ዘርፎችም በቀጣይ እያሰለጠን ሰራተኞች ተመዝነው ደረጃቸው እንዲሻሻል ከማድረግ ባሻገር እውቀትና ክህሎታቸውም እንዲያድግ ለማድረግ እቅድ ተይዟል ያሉት ም/ፕሬዚዳንቱ ሌሎች የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችም ይህን እንደ ተሞክሮ ቢወስዱት መልካም እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡

ስራው እንዲሳካ ብዙ ጥረት ላደረጉ የተማሪዎች አገልግሎት የስራ ሓላፊዎችም ምስጋና አቅርበዋል አቶ ብርሀኑ፡፡

የተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ፍቅሬ አልማው በበኩላቸው የተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ይሰራል ለአብነትም፡- ለተማሪዎች የምክር አገልግሎት፤ የምግብ አገልግሎት፤ የመኝታ አገልግሎት፤ ስፖርትና የመዝናኛ አገልግሎቶችን በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለምግብ ቤት ሰራተኞች ስልጠና በመስጠት እየሰራ ያለው ስራ ትልቅ ስኬት ነው፡፡ በተለይም ለረጅም አመታት እንጀራ እየጋገሩ፤ ወጥ እየሰሩ ዩኒቨርሲቲውን ከዚህ ላደረሱት እናቶች ምስጋና ይገባል፡፡ ይህን ስራ ለማሳካት ከተለያዩ ባለ ድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር ጥረት ላደረጉት የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ሁሉ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል ወ/ሮ ፍቅሬ፡፡

በቀጣይም በዝቅተኛ የስራ ደረጃ ላይ የሚገኙ ሰራተኞችን በማሰልጠን የተሻለ እውቀትና ክህሎት እንዲኖራቸው፤ ደረጃቸው እንዲሻሻል እንሰራለን ብለዋል ወ/ሮ ፍቅሬ አልማው፡፡

በዋናው ግቢ ወጥ ቤት የሚሰሩት ወ/ሮ ትዕግስት አወቀ እንደገለጹት በተሰጠን ስልጠና ተደስቻለሁ፡፡ በዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ካምፓሶች በመከፈታቸው ቀደም ሲል የነበረው የስራ ጫና በአንጻራዊነት ሲታይ ተቃሏል ሆኖም ግን የስራው ባህሪ በጣም አድካሚና ለጤና ችግርም ተጋላጭ እያደረገን ስለሆነ ለስራው ክብደትና ለድካማችን የሚመጥን ደረጃና ደምወዝ እንዲሻሻል ሊደረግ ይገባል ብለዋል፡፡

በቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የምግብ ቤት ፈረቃ ሺፍት አስተባባሪ ሆነው የሚሰሩት ወ/ሮ አበቡ እውነቴ በበኩላቸው አንድ ወር ከ15 ቀን የፈጀ የምግብ ዝግጅት ስልጠና እንደወሰዱና የሲኦሲ ፈተናም ተፈትነው በማለፋቸው የተደሰቱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ስልጠናውን በግል ለመሰልጠንና ሲኦሲ ለመፈተን አቅም ስለሌለን በግል ከፍሎ መሰልጠን የማይታሰብ ነበር ያሉት ወ/ሮ አበቡ ዩኒቨርሲቲው ክፍያውን ሁሉ ሸፍኖ ስላሰለጠነን እጅግ በጣም እናመሰግናለን ብለዋል፡፡

ለ32 አመታት ያክል በትጋት ያገለገሉት አንጋፋዋ የወጥ ቤት ባለሙያ ወ/ሮ የሺ ወርቅ ቦጋለ ስልጠናውን የሰጡት መምህራኖች በጣም ጎበዞች ናቸው በተግባር የተደገፈ ስልጠና ነው የተሰጠን ለዚህም ዩኒቨርሲቲያችን እናመሰግናለን ብለዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው የግቢ ውበት ላይ እየሰራ ያለው ስራ የሚያኮራ ነው በቀጣይ ግን ቋሚ አትክልትና ፍራፍሬዎችን መትከል ላይ ትኩረት ተደርጎ ቢሰራ ውበቱም ጥቅሙም ቀጣይነት እንዲኖረው ማድረግ ያስችላል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ሌላዋ በባሕር ዳር ቴክኖሎጅ ተቋም (ፖሊ ግቢ) ለ34 አመታት ያክል በትጋት ያገለገሉት አንጋፋዋ የወጥ ቤት ሽፍት አስተባባሪ ወ/ሮ የካባ ብርሀኑ በዩኒቨርሲቲው ሰርተው፣ ወልደው፣ ከብደው፣ ወግ ማዕረግ ያዩበት በመሆኑ እንደቤታቸው የሚቆጥሩት እና የሚወዱት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በባሕር ዳር ቴክኖሎጅ ተቋም የምግብ ቤት አስተባባሪ የሆኑት ወ/ሮ ሰናይት ባለው በበኩላቸው ሰራተኞቹ ስልጠና በማግኘታቸው የስራ ተነሳሽነታቸው ጨምሯል ብለዋል፡፡  በስልጠናው የተሳተፉ ሁሉም ሰራተኞች ስልጠና በማግኘታቸው መደሰታቸውን የተናገሩ ሲሆን ሁሉም ሰራተኞች ያነሱት የጋራ ጥያቄ ደረጃና ደምወዛችን ቢሻሻል የሚል ሀሳብ አንስተዋል፡፡

 

2ኛው የታዳጊ ህፃናት ፕሮጀክት ዓመታዊ የምዘና ውድድር ተጠናቀቀ

[ጳጉሜ 04/2014 ዓ/ም፤ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ባዳዩ] 

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት በባሕር ዳር እና አካባቢው የሚገኙ የታዳጊ ስፖርት ፕሮጀክቶች የሚሳተፉበት 2ኛው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የታዳጊ ህፃናት ዓመታዊ ምዘና ከነሐሴ 22 እስከ ጳጉሜ 3 በተለያዩ የስፖርት አይነቶች ሲካሄድ የቆየው ውድድር ተጠናቀቀ ፡፡

ውድድሩ በእግር ኳስ፣ በሜዳ ቴንስ እና በባድሜንተን ሲደረግ፤ 15 የእግር ኳስ ፕሮጀክት ክለቦችን በማሳተፍ ከፍተኛ ፉክክር ተደርጎበታል፡፡ በዚህም የተመልካችን ስሜት የገዛው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ከ16ዓመት በታች የወንዶች እግር ኳስ ቡድን እና የአሀዱ እግር ኳስ ፕሮጀክት ቡድን የዋንጫ ጨዋታ አድርገው የአሃዱ ቡድን የባሕር   ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ እግር ኳስ ፕሮጀክት አቻውን  2ለ1 በማሸነፍ ለ2ኛው የታዳጊ ህፃናት ፕሮጀክት ውድድር የተዘጋጀውን ዋንጫ አንስቷል፡፡በዕለቱ የተዘጋጀውን የፀባይ ዋንጫ የሰባታሚ ፕሮጀክት እግር ኳስ ሰፖርት ቡድን መውሰድ ችሏል፡፡

በውድድሩ ለደረጃ የተጫወቱት አደይ አበባ እና ልደታ የህፃናት ፕሮጀክት ቡድኖች ሲሆኑ አደይ አበባ ተጋጣሚውን 5ለ1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

በእግር ኳስ ጨዋታው ጠንካራ ተወዳዳሪ የነበረው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ከ16 ዓመት በታች የወንዶች እግር ኳስ ቡድን 2ኛ በመውጣት የብር መዳሊያ፣ 3ኛ የወጣው አደይ አበባ ፕሮጀክት ስፖርት ቡድን የነሐስ ሜዳልያ ወስደዋል፡፡

በጨዋታው ከተመልካች እና ከስፖርት ባለሙያዎች በተሰበሰበ መረጃ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ከ16    ዓመት በታች ወንዶች እግር ኳስ ቡድን ኮከብ አጥቂ እና ኮከብ ግብ ጠባቂ ተጫዋቾችን ሲያስመርጥ፤ የዕለቱ ኮከብ   ተጫዋች ከአሀዱ የፕሮጀክት ቡድን ተመርጧል፡፡

መርሃ ግብሩ በቆየባቸው ከነሐሴ 22 እስከ ጳጉሜ 3/2014 ዓ.ም ጉልህ አስተዋፆ ላበረከቱ የስፖርት ቤተሰቦች ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች እና ከፍተኛ ባለሙያዎች እጅ የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል፡፡

ለጡረተኞች የምግብ እህል በስጦታ ተበረከተላቸው

[ጳጉሜ 04/2014 ዓ/ም፤ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ] የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ በቆጋ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ቦታ ላይ ያመረተውን 130 ኩንታል እህል ከዩኒቨርሲቲው በተለያየ ጊዜ በጡረታ ለተገለሉና አነስተኛ ገቢ ላላቸው አቅመ ደካሞች በስጦታ አበርክቷል::

የኮሌጁ የድህረ ምረቃ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ዲን ዶ/ር ተስፋየ መላክ እንደገለፁት በቆጋ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ስፍራ አብላጫው  ስራ ለምርምርና የዘር ብዜትን ለማስፋፋት ሆኖ ከዚህ ዓላማ የተረፈው መሬት የሚያመርተው ምርት ለተለያዩ የማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎች ማለትም ከአሁን በፊት ፍላጉት ላላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለሽያጭ ማቅረባቸውንና ከ125 ኩንታል በላይ የሚሆን እህል በተለያየ ጊዜ በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ዜጎች መስጠታቸውን ተናግረዋል፡፡

ዶ/ር ተስፋየ በማስከተልም ዛሬ የተሰጠው 130 ኩንታል እህል 121 ኩንታል ስንዴ፣ 4 ኩንታል ጤፍ እና 5 ኩንታል የዳጉሳ ምርት ሲሆን የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ውሳኔ አሳርፈውበት በጡረታ ከተገለሉት ሰዎች መካከል አነስተኛ ገቢ ያላቸውና አቅመ ደካሞችን ለይቶ ስም ዝርዝራቸውን ለኮሌጁ በላከው መሰረት ለጡረተኞች የኮሌጁ ዲን ዶ/ር አሳምነው ጣሰው አስረክበዋል፡፡

ኮሌጁ እህሉን ሲያስረክብ ጡረተኞች እንዳይንገላቱ በማሰብ በዩኒቨርሲቲው ተሽከርካሪ እስከ ቤታቸው ድረስ በማጓጓዝ አኩሪ ተግባር አከናውኗል፡፡

 

ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:- https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

#BDU60th_ANNIVERSARY

 

Bahir Dar University STEM center graduates students who have been attending hands- on training in the summer outreach program. The students who were selected from government and private schools from Bahir Dar on merit basis have been receiving hands-on training for 45 days.

While introducing the day’s program Dr. Alemu Tesfaye vice Director of the center said that the center provides other similar programs/trainings like Science Shared Camp, Summer Camp, Girls’ Camp, Project Work, Weekends, Lab Works. Dr. Alemu noted that although the center encourages students from government schools to receive the trainings, due mainly to transportation problem, many couldn’t, so the regional education bureau shall plan to cover the students’ transport fee for a more pronounced impact of the training offered by the center.

Dr. Tesfaye Shiferaw, V/President for Research and Community Services of Bahir Dar University in the certificate handover ceremony for the trainees recalled that the center has so far contributed in training more than 3,090 students since 2012. Dr. Tesfaye added students who have taken the training shall share their training experience to their fellow students when they are back to their schools.

A national conference on Reforming Ethiopia’s Tax and Tort Laws held

Bahir Dar University conducted National research conference in collaboration with USAID Justice Activity on the theme: Reforming Ethiopia’s Tax and Tort Laws that focuses on different researches conducted on the Ethiopian tax system and tort Laws on August 31/ 2022. 

The research conference is conducted with the objective of generating evidence-based input for the law reform process.This conference is part of BDU Law School and USAID Justice (Feteh) Activity collaborative efforts to provide evidence-based input for the law-making organ to implement informed Tax and Tort law reform. In this one-day Conference, seven research papers that focus on tax and tort law reform were presented.  The papers touches issues related to income tax, property tax, tax dispute resolution, tax enforcement mechanism and institutional framework, and the adequacy and sufficiency of Ethiopian tort law. It is strongly believed that the papers will trigger discussions and serve as valuable input for the tort and tax law reform process. The conference brought together a number of key actors not only from academia but also from lawmakers, law enforcement organs, the judiciary, the private sector and civil society.

The papers presented entailed constructive discussions that enable the researchers to get valuable input to be able to upgrade their research works. The majority of the participants from different government organs and the private sector affirm the timeliness of the conference and they also expressed their belief that the findings of the research works will contribute immensely to the law reform process.

 

 

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ 2ኛውን የታዳጊ ወንዶች እግር ኳስ ውድድር ማካሄድ ጀመረ

 [ነሐሴ 24/2014 ዓ/ም፤ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ]

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት ባሕር ዳር እና አካባቢው የሚገኙ የታዳጊ ወንድ እግር ኳስ ፕሮጀክቶች የሚሳተፉበት 2ኛው የምዘና ውድድር በዩኒቨርሲቲው ስፖርት አካዳሚ በድምቀት መካሄድ ተጀምሯል።

በ15 የፕሮጀክት ተሳታፊ ቡድኖች መካከል የተጀመረው የእለቱ ውድድር ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲን ከሰባታሚት ቀበሌ አገናኝቷል። በውድድሩም የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሳባታሚት አቻውን 5 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፉ ድል ቀንቶታል።

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የባሕር ዳር ከተማ የፕሮጀክቶች የምዘና ውድድር አስተባባሪ እና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ታዳጊ ፕሮጀክት አሰልጣኝ አቶ ዳንኤል ጌትነት የውድድሩን አላማ ሲናገሩ አመቱን ሙሉ እግር ኳስ ሲጫወቱ ለነበሩ ህፃናት የውድድር እድል መፍጠር፣ አሰልጣኞች ያላቸውን ጠንካራ እና ደካማ ጎን የሚመዝኑበት፣ ልጆችም የውድድር ልምድ እና ጫናን መቋቋም እንዲችሉ በማድረግ አስተዋፅኦው የጎላ እንደሆነ ገልጸው ውድድሩ እስከ ጳጉሜ 3 ድረስ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

አቶ ዳንኤል ይህ ውድድር ለሁለተኛ ጊዜ የተደረገ ሲሆን በቀጣይ አመት አመቱን ሙሉ በሳምንት ሁለት ቀን እየተጫወቱ ምዘና በማካሄድ ጎን ለጎን ደግሞ ስልጠና ይሰጣቸዋል ብለዋል፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ የእግር ኳስ መምህር እና የአለም አቀፍ እግር ኳስ ዳኛ ዶ/ር ኃይለ እየሱስ ባዘዘው በበኩላቸው ውድድሩ በ15 ክለቦች ከ16 ዓመት በታች የሚደረግ የታዳጊ ወጣቶች እግር ኳስ ውድድር መሆኑን ጠቁመው፤ በከተማው ውስጥ በፕሮጀክት ታቅፈው ለሚሰለጥኑ ከ20 በላይ ክለቦች ቢያንስ በአመት አንድ ጊዜ ከተማው ውስጥ የሚደረገውን የታዳጊዎች መተካካት ሊያግዝ ይችላል በሚል  መጀመሩን ገልፀውልናል፡፡

ዶ/ር ኃይለ እየሱስ ውድድሩ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማሩ ባሻገር ማህበረሰቡን ከማገልገል አንጻር ከ300 በላይ የሚሆኑ ታዳጊ ወጣቶች ክረምቱን በውድድር እንዲያሳልፉ የአካዳሚው መምህራን የዳኝነት ስልጠና በመውሰድ ለታዳጊዎቹ የሚያደርጉት እገዛ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡

በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የአደይ አበባ የፕሮጀክት አሰልጣኝ አቶ ሞገስ ቀለምወርቅ ቡድናቸው በዚህ አመት አማራ ክልል ባዘጋጀው የፕሮጀክት ሙከራ ላይ አራተኛ ሆኖ እንዳጠናቀቀ እና ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እያካሄደ ባለው ከ16 ዓመት በታች ውድድር እየተሳተፈ ይገኛል ብለዋል፡፡ በዚህ ውድድር ታዳጊዎች በምን ደረጃ እንደሚገኙ የምንመዝንበት የአቋም መፈተሻ እና እኛም አሰልጣኞች ምን ያህል አሰለጠን የሚለውን የምንለካበት ነው ብለዋል፡፡

በውድድሩም የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዚደንት ዶ/ር ተስፋዬ  ሽፈራው፣ የባሕር ዳር ከነማ ዋና አሰልጣኝ ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ፣ ከባሕር ዳር ከተማ እግር ኳስ ፌደሬሽን አቶ ዳግማዊ፣ ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ዶ/ር ዘላለም እንዲሁም የስፖርት አካዳሚ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዶ/ር ተከተል በመገኘት ታዳጊ ተወዳዳሪዎችን  በማበረታታት ውድድሩን አስጀምረዋል።

  ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ- ባዳዩ-BDU

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

Thank you for visiting, inviting and sharing our Pages!

Thank you for your likes and comments!

ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:-https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

 

የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተማሪዎች የመጀመሪያው የጎዳና ላይ ፋሽን ትርኢት ቀረበ

***********************************************

[ነሐሴ 21/2014 ዓ/ም፤ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ]

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የ2014 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች ከሰባት በላይ በሆኑ የፈጠራ ዲዛይኖች የተሰሩ አልባሳትና ልዩ ልዩ ማስጌጫዎች የተዘጋጀ እና በአገራችን የመጀመሪያ የሆነ የተማሪዎች የጎዳና ላይ ፋሽን ትርኢት በውቢቷ ባሕር ዳር ከተማ አቅርበዋል:፡

ዝግጅቱን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ብርሃን ሀይሉ ተቋሙ በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን ትርኢት ማዘጋጀቱ ለከተማውም ሆነ በዘርፉ ላሉ አካላት ትልቅ ምዕራፍ መክፈቱን ተናግረዋል፡፡ ኩነቱም በፋሽን ቴክኖሎጂ ላይ ያተኮረ በመሆኑ የአገራችንን ቴክስታይልና አልባሳት ኢንዱስትሪን በማሳደግ ረገድና የስራ ዕድል በመፍጠር ትልቅ አስተዋጾ እንዳለው ይታመናል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶ/ር ታምራት ተስፋዬ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በ24 ፕሮግራሞች የፒኤች ዲ፣ የሁለተኛ ዲግሪ አና በመጀመሪያ ዲግሪ ደረጃ በማስተማር የባሕር ዳር ከተማን የፋሽን ከተማ ለማድረግ አልሞ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

ዶ/ር ታምራት አክለውም እነዚህ በትርኢቱ ላይ የምታዯቸው ተመራቂዎቻችን በሀገሪቱ ውስጥ ተሰማርተው ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪን ለማዘመን የሚሰሩ ልጆቻችን ናቸው ብለዋል፡፡ በዚህም ኢንስቲትዩቱ ከሚያስመርቃቸው 26% የራሳቸውን ስራ ፈጥረው የሚሰሩ ሲሆን ከ85% በላይ የሚሆኑት ደግሞ በተመረቁበት ሙያ የስራ ዕድል ማግኘታቸው እንደ ሀገር የመጀመሪያው ኢንስቲትዩት ያደርገናል ብለዋል፡፡

የዕለቱን ፕሮግራም ያስተባበሩት የፋሽን ዲዛይን ትምህርት ክፍል ኃላፊ መምህር ሰላማዊት መላኩ ተመራቂ ተማሪዎች ሀገር በቀል የሆኑ እና የውጪውን አልባሳት በማቀናጀት ያላቸውን የፈጠራ ስራ በማሳየታቸው ተቋሙንም ሆነ ዩኒቨርሲቲውን ለማህበረሰቡ በማስተዋወቅ ረገድ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በፋሽን ትርኢት ስነ-ስርዓቱ ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቦርድ አባላት እና የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች እንዲሁም የከተማው ማህበረሰብ ታድመውበታል፡፡ የፋሽን ትርኢቱም ከስካይ ላይት ሆቴል እስከ ዩኒሰን ሆቴል ባለው የጎዳና መንገድ ላይ የተካሄደ ነበር፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ- ባዳዩ-BDU

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

Thank you for visiting, inviting and sharing our Pages!

Thank you for your likes and comments!

ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official

Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt

LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university

Twitter: - https://twitter.com/bdueduet

Tiktok:-https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL

website :- www.bdu.edu.et

 

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በድምቀት አስመረቀ
=============================================
[ነሐሴ 21/2014 ዓ/ም፤ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ -ባዳዩ] የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ፣ በሁለተኛ ፣በሦስተኛ ድግሪ፣ በPGDT፣ በHDP እና በማሪታይም ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 4ሺህ 616 ወንድ እና 1ሺህ 900 ሴት በድምሩ 6 ሺህ 515 ተማሪዎችን ዛሬ ነሃሴ 21 /2014 ዓ.ም በድምቀት አስመረቀ፡፡
 
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲን ለ60ኛ ዓመት ያበቃው እና ዩኒቨርሲቲውን ከመሰረቱት ሁለት የትምህርት ተቋማት አንዱ የሆነው የቀድሞው ፖሊ ቴክኒክ ኢንስቲትዩት የአሁኑ የባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ተቋም በዓለም አቀፍ ደረጃ በአራቱ የምህንድስና መርሐ-ግብሮች በኬሚካል፣ በሲቪል፣ በኤሌክትሪካልና በሜካኒካል ምህንድስና ዘርፎች ዕውቅና ለመሰጠት የመጀመሪያውን ዙር ማጣሪያ አልፎ ሁለተኛውን እና የመጨረሻውን ዙር በመጠባበቅ ላይ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ውጤቱ ዩኒቨርሲቲውን ከሰሃራ በታች ከሚገኙ ሀገራት የመጀመሪያው እንደሚያደርገውም ገልፀዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ አክለውም ከፖሊ ቴክኒክ ኢንስቲትዩት አድጎ የወጣው የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በያዝነው ዓመት 15 መመዘኛዎችን አልፎ ሁለት ቤተ-ሙከራዎችን ዕውቅና በማሰጠት የማስተማሪያ ፋብሪካ ፅንሰ ሐሳብን ተግባር ላይ ማዋሉን ገልፀው ተቋሙ የሰራው ጠንካራ ስራ በሀገሪቱ ብሎም በምሥራቅ አፍሪካ ቀዳሚ እንደሚያደርገው በመግለፅ ለዕለቱ ተመራቂ ተማሪዎች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
 
በተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙት የዕለቱ የክብር እንግዳና በኢትዮጵያ፣ በጅቡቲና በአፍሪካ ኅብረት የኢንዶኔዥያ አምባሳደር አል ቡሲራ ባስኑር ለዕለቱ ተመራቂ ተማሪዎች በመልዕክታቸው “ የዛሬ ተመራቂዎች ምንም እንኳን ከቤተሰቦቻችሁ ብትወጡም የቤተሰቦቻችሁ ብቻ አይደላችሁም፤ የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ብቻም አይደላችሁም፤ የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጭምር ሃብት ናችሁ ሲሉ ተናግረዋል ”፡፡ ኢንዶኔዝያ እና ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ ትብብር እያደረጉ ከ60 ዓመት በላይ መቆየታቸውን ተናግረው በትምህርት ዘርፍ ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር እየሰሯቸው ያሉ የሁለትዮሽ የትብብር ስራዎች ጉልህ ማሳያ መኾናቸውን አምባሳደሩ ጠቁመዋል ፡፡ ትምህርት የሁሉ ነገር መፍቻ ቁልፍ ነው ያሉት አምባሳደሩ የዛሬ ተመራቂ ተማሪዎችን እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል፡፡
 
ዩኒቨርሲቲው ባሳለፍነው ዓመት ለሀገራችን ኢትዮጵያ በማህበረሰብ አገልግሎት ጉልህ አስተዋፆ ላበረከቱት ለብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሰሜን ወሎ እና በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኦሮሚያ ልዩ ዞን ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል፤ እንዲሁም በስፖርቱ ዘርፍ በጎ ስራ ለሰራችው ለኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ የክብር ዶክትሬት ማዕረግ የሰጠ ሲሆን ከኢንዶኔዥያ አምባሳደር አል ቡሲራ እና ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ እጅ ተቀብለዋል፡፡
 
ብጹዕ አቡነ ኤርምያስ ለሀዋሪያዊ ተልኮ ከሀገር ውጭ ቢሆኑም ካሉበት ሀገር ኾነው ባስተላለፉት የቪዲዮ መልዕክት የተሰጠው የክብር ዶክትሬት ለእኔ ሳይሆን በጸሎት ሲጠብቁኝ ለነበሩት ለብጹዕ አቡነ ቄርሎስ፣ ከጎኔ ኾነው በምክር ለረዱኝ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ለሚፋጠኑት ካህናት፣ ዲያቆናት፣ ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ ጋር ድልድይ ኾነው ላገናኙኝ የመስጊድ ኮሚቴ አባላት፣ ሰብዓዊ ግዴታቸውን ለተወጡ አባቶቻችን እና እናቶቻችን ነው ሲሉ ተናግረዋል።
 
አልተማሩም ያልናቸው ወገኖቻችን በመስዋእትነት ያቆዯትን ሀገራችንን ተማርን ያሉ ሰዎች በየቀኑ የመለያየት፣ የማፍረስ ፈጠራ እየፈጠሩ ወገንን ከወገን ሲለያዩ፣ የተገነባውን ሲያፈርሱ እየተመለከትን ነው ብለዋል። የጥፋት ተቃራኒ የሆነውን ልማት እንድታለሙ፣ ራሳችሁን ረድታችሁ ሀገራችሁን እንድትረዱ፣ አንድ የሆነችው ሀገራችሁና ሕዝባችሁ በአንድነቱ እንዲቀጥል አደራ ሲሉ በአፅንዖት ተናግረዋል።
 
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የክብር ዶክተር ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተሰጣት የክብር ዶክትሬት ለእሷ ብቻ ሳይኾን በአትሌቲክሱ ዘርፉ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፉ አደባባይ ስሟን ለሚያስጠሩ አትሌቶችና አሰልጣኞች እንዲሁም ለአትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ ከፍተኛ ሞራልና መነሳሳትን ይፈጥራል ስትል ተናግራለች ፡፡ የክብር ዶክተር ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ተመራቂዎች በዩኒቨርሲቲ የቀሰሙትን እውቀት ተጠቅመው ሀገራቸውን በቅንነትና በታማኝነት እንዲያገለግሉ ስትል መልዕክት አስተላልፋለች ፡፡
 
በ2014 ዓ.ም የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ በትምህርታቸው አብላጫ ውጤት ላስመዘገቡ እና ከሁሉም ግቢ ለተውጣጡ ተማሪዎች የምስክር ወረቀት፣ የሜዳሊያ እና የዋንጫ ሽልማታቸውን ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት እና ከአካዳሚክ ጉዳዩች ም/ፕሬዚዳንት እጅ ተቀብለዋል፡፡
 
በመጨረሻም በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የስራ አመራር ቦርድ አባላት፣ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ዶ/ር የሺመብራት መርሻ፣ ፕሮፌሰር ማስረሻ ፈጠነ የBiT እና EiTEX አማካሪ ቦርድ የባሕር ዳር ከተማ ተቀዳሚ ም/ከንቲባና የዩኒቨርሲቲው ቦርድ አባል ዶ/ር ድረስ ሳህሉ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
 
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ- ባዳዩ-BDU
ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ
Wisdom at the source of Blue Nile
Thank you for visiting, inviting and sharing our Pages!
Thank you for your likes and comments!
ለተጨማሪመረጃዎች፡-
Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official
website :- www.bdu.edu.et

Pages