Latest News

Seven candidates have been identified by the President Election Committee, and Bahir Dar University warmly congratulates you all for being selected for further examination in the run up to the Office of Presidency for the Next Term!!!

BDU’s College of Medicine and Health Science has graduated its 5th batch Medical doctors in a joyful ceremony held at Peda Campus, Auditorium Hall.

Out of a total of 158 graduates, 146 were Medical Doctors who pursued their studies here at BDU for the last six year. 7 students were also graduated in masters degree in Medical parasitology and the remaining 5 were specialists in General Surgery program.  

In the ceremony, recognition was given to personalities from pediatric, internal medicine, and general surgery departments of the college for their outstanding contribution and service.  Award and recognition was also conferred to “Human Bridge” for its contribution in supplying medical equipments to BDU’s new teaching referral hospital.

Guest honor of the ceremony Dr. Birhanu Nega from Ethiopian Medical Association, Dr. Baylie Damtie and other guests have attended the graduation.

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጂኦግራፊና የስነ-ህዝብ ጥናት ትምህርት ክፍል ወጣቱን ለልማት በመጠቀም አስፈላጊነት ላይ የተመሰረተ ለሁለት ቀን የሚቆይ አገር አቀፍ ጉባኤ አካሂዷል። ሀገሪችን ኢትዮጵያ ሆነ አህጉራችን 60 ፐርሰንት የሚሆነው ወጣት እንደሆነና ይህን የህዝብ ፀጋነቱን በመጠቀም ኢንቨስት ማድረግና መጠቀም እንደሚገባ የተናገሩት በመርሀ ግብሩ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶ/ር ሙሉነሽ አበበ ናቸው። ኢትዮጵያ በወጣት የታደለች ሀገር እንደሆነችና ይህንን ወጣት ኃይል ለልማት በመጠቀም ፀጋ ወይም ጥሩ አጋጣሚ ሲሆን ካልተጠቀምንበት ግን እዳ ሊሆን እንደሚችልና ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ወጣቱ ላይ ኢንቨስት በማድረግ በእድገት ጎዳና እንደተራመዱና በአሁኑ ወቅት ትልቅ የእድገት ማማ ላይ እንደሚገኙና በተለይም ትምህርትን፣ ጤናን፣ ኢኮኖሚን፣ ፈጠራን አጣምረው በመስራታቸው ውጤታማ እንደሆኑና በተቃራኒው ደግሞ ይህን የወጣት ክፍል አቀናጅተው ያልተጠቀሙ ሀገሮች እስከ አሁን ድረስ በድህነት ላይ እንደሚገኙ ነገር ግን ሀገራችን ኢትዮጵያም ሆነች አህጉራችን አሁን ትኩስ ሀይል እንዳላቸውና ይህን ሀይል ወደ አምራች ፀጋ ለማድረግ ወጣቶች ላይ ኢንቨስት ማድረግ፣ በትክክል መምራትና መጠቀም እንደሚያስፈልግ ምክትል ፕሬዝዳንቷ ገለፀዋል። ከዚህም በተጨማሪ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በትምህርት፣ በጤና እንዲሁም በኢኮኖሚ ላይ ብዙ ኢንቨስት እንዳደረገችና በዚህም ምክንያት ብዙ ጥቅሞች እንደተገኙበትና ከዚህ በላይ መስራት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል። የስነ-ህዝብ ጥሩ አጋጣሚ መጠቀም ለሀገር እድገት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለውና የስነ- ተዋልዶ ቁጥጥርን በመጨመር የህጻናትን እድሜ በመቀነስ ከ15 ዓመት በላይ ያሉ ወጣቶችን በትምህርት፣ በጤና፣ በፈጠራ፣ በኢኮኖሚ፣ እንዲሁም በቴክኖሎጂ እንዲበለጽጉ በማድረግ ወጣቱን መጠቀምና የሀገሪቱን እድገት ወደ ተሻለ ጎዳና መውሰድ እንደሚቻልና በአሁኑ ወቅት በሀገራችን ኢትዮጵያ ከ30 አመት እድሜ ክልል በታች የሚሆነው ወጣት 50 ሚሊዮን እንደሚሆንና ይህም ጥሩ አጋጣሚ እንደሆነ የገለጹት የመርሀ ግብሩ ዋና አዘጋጅ የሆኑት ዶ/ር አማረ ሰውነት ናቸው። ዶ/ር አማረ አክለውም በዚህ ጉባኤ ላይ ከኮሪያ፣ ከቬትናም፣ ከአሜሪካ፣ ከኬንያ እንዲሁም ከሀገር ውስጥ 13 ዩኒቨርሲቲዎች እና ከሁሉም ክልሎች ተሳታፊ እንደሆኑና ከ40 በላይ ጥናታዊ ጽሁፎች እንደሚቀረቡና የተለያዩ ልምዶች እንደሚገኙበት እንዲሁም የተገኘውን ልምድ በመሰነድ ለሚመለከተው አካል እንደሚሰጡና ለተፈጻሚነቱም ክትትል እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። ሀገሪቱ ባለፉት 15 አመታት በሁሉም ዘርፍ ትልቅ ለውጥ እንዳሳየችና የስነ-ህዝብ ስራ የትምህርት፣ የጤናና የኢኮኖሚ ድምር ውጤት እንደሆና አሁን ሀገሪቱ እየተከተለች ያለችው የትምህርት፣ የጤናና የኢኮኖሚ ስራ የስነ-ህዝብ ስራውን እያቀለጠፈው እንደሚገኝ የገለጹት በመርሀ ግብሩ መዝጊያ ስነ-ስርዓት ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ይናገር ደሴ ናቸው። ከዚህ በተጨማሪ ባለፉት አመታት በመንግስት በተሰራ ስራ በርካታ ወጣቶች ተጠቃሚ እንደሆኑና የዚህ እድል ተጠቃሚ ያልሆኑ ወጣቶች በተለያየ ምክንያት በመኖራቸው ባለፈው አመት እነዚህን ወጣቶች በገጠርም ሆነ በከተማ ተጠቃሚ የሚያደርግ የወጣቶች ፈንድ በማቋቋም እየተሰራ እንደሚገኝም ነው ኮሚሽነሩ የገለጹት።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ISSD) የክልሉ አርሶ አደሮች ጥራት ያለው ዘር
እንዲያገኙ እና የምግብ ዋስትና እንዲረጋገጥ ከአማራ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲት፣ ከአዴት ግብርና ምርምር፣
ከአማራ ክልል ግብርና ቢሮ እንዲሁም በዘርፉ ተሰማርተው ከሚሰሩ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ እየሰራ ይገኛል፡፡
በመስክ ምልከታው ወቅት ከባሕር ዳር ፣ከጎንደር ፤ከደብረ ታቦር ፤ከደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲዎች እንዲሁም
ከምዕራብ ጎጃም፤ ከአዊ፤ከምስራቅ ጎጃም፤ከሰሜን ጎንደር፤ከደቡብ ጎንደር ፤ከሰሜን ወሎ ዞኖች የሚመለከታቸው
ባለሙያዎች፣ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም በክልሉ ውስጥ በዘር ዘርፍ ላይ የሚሰሩ የሥራ ክፍሎች በመስክ ምልከታው
ወቅት ተገኝተዋል፡፡
በሰሜን አቸፈር ወረዳ ሳንክራ ቀበሌ ላይ በተደረገው የመስክ ምልከታ ላይ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ እና
የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ISSD/ አስተባባሪ የሆኑት
ዶ/ር ደረጀ አያሌው የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ISSD) በዋነኛነት የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ ከማገዝ
አኳያና የዘር ስርዓትን ለማሻሻል ከዛሬ 7 ዓመት በፊት የተቋቋመ እንደሆነ እና በክልሉ ባለፉት ስድስት ዓመት ውስጥ
የተሻሉና ጥራት አላቸው ተብለው የተመረጡ ዘሮችን በማባዛት በክልሉ ውሥጥ እንዲሁም ከክልሉ ውጭ ምርትና
ምርታማነትን ከፍ ማድረግ ላይ እየሰራ እንደነበር እና እያደገ የመጣውን ማህበረሰብ ለመመገብ ከፍተኛ የሆኑ ስራዎች
ሲሰራ እንደቆየ ጠቁመው አሁንም የውል ጊዜውን ለሶስተኛ ጊዜ በማራዘም ከዚህ በፊት ያልተነኩ ስራዎችን
ለመስራትና ከዚህ በፊት ትኩረት ሳይሰጠው የቆየውን የኢ-መደበኛወን የዘር ሥርዓት ለመደገፍ እየሰራ እንደሆነና በተለይ
በዚህኛው ዙር ሴት አርሶ አደሮችን በተለየ ሁኔታ ለመደገፍ እያመቻቸ የቆየ ቢሆንም በዚህ ዓመት ግን ወደተግባር
እንደተገባ ተገልጿል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮግራም በኔዘርላንድ መንግስት የሚደገፍ ሆኖ
በኢትዮጵያ ላይ በሚገኙ አራት የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማለትም ባሕር ዳር፣ ሀሮምያ፣ ሐዋሳ፣ መቀሌ
ዩኒቨርስቲ እንዲሁም የኦሮሚያ የዘር ልማት ኢንተርፕራይዝ ጋር በመተባበር በሀገሪቱ ላይ የሚታየውን የዘር ብዜት ችግር
ለመቅረፍ እየሰራ እንደሚገኝ እና ማዕከላቱ ለማሕበራት፣ ለግል ዘር አባዦች እንዲሁም ለዘርፍ ባለሙያዎች
የስልጠና፣ የልምድ ልውውጥ፣ የገንዘብ እርዳታ፣ የምክክር መድረክ ማዘጋጀት፣ ማስተዋወቅና የምርምር አገልግሎት
በዋነኛነት ሲሰጡ እንደቆየና አሁንም እየሰጠ እንደሚገኝ አስተባባሪው ገለፀዋል፡፡
የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ISSD) ከስድስት ወረዳዎች 1200 አርሶ አደሮች
በመምረጥ የአጭር ጊዜ ስልጠና በመስጠጥ ወደ ስራ እንዲገቡ የተደረገ ሲሆን 1195 ወደ ስራው ሲገቡ 5 ያህሉ
በተለያየ ምክንያት ወደ ስራ ሳይገቡ እንደቀሩ ጠቁመው በአሁኑ ወቅት ፕሮጀክቱ በዳጉሳ፣
በስንዴ፣በጤፍ፣በቆሎ፣በአተር፣በገብስ፣ማሽላ ወዘተ የሰብል ዝርያዎች ላይ እየሰራ እንደሆነ ገልጸው በተለይ የዳጉሳን
ምርት ላማሳደግ 19 የዳጉሳ ዝርያወችን በማቅረብ ለእያንዳንዱ አርሶ አደር 3 የዳጉሳ ዝርያዎችን በመዝራት የትኛው
የተሸለ እና ምርታማ እንደሆነ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ መለየት እና በሚቀጥለው ዓመት የበለጠ በማጠንከር ለመስራት
እየተዘጋጁ እንደሆነ የገለፁት የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ISSD) ህብረት ስራ ባለሙያ የሆነው አቶ ሚኒሊክ
ከፋለ ናቸው፡፡ ባለሙያው አክለውም አርሶ አደሮችን በማሳተፍ በኤክስቴሽኑ መርኀ ግበር ላይ ያልተካተቱ ነገር ግን
የማህበረሰቡን የኑሮ ደረጃ ከፍ ሊያደርጉ የሚችሉ ሰብሎች ላይ ትኩረት አደርገው እንደሚሰሩ ጠቁመዋል፡፡

2

በሰሜን አቸፈር ወረዳ በሰብልም ሆነ በምርት ሽፋን ከበቆሎ ቀጥሎ በሁተኛ ደረጃ የሚገኘውን የዳጉሳ ዝርያ ማህበረሰቡ
እንደ ጤፍ፣ስንዴ ወዘተ በመደበኛው የዘር ስርዓት ዘር የማይቀርብለት በመሆኑ እስከ አሁን ድርስ ተጠቃሚ ሳይሆን
እንደቆየ እና ነገር ግን ይህን ችግር በመረዳት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮግራም /ISSD/
ለመስራት እያደረገ ያለው ጥረት ሊደነቅ እንደሚገባ የተናገሩት የሰሜን አቸፈር ወረዳ የሰብል ባለሙያ የሆኑት አቶ ዘመነ
ወርቁ ናቸው ፡፡
በመስክ ምልከታው ከሰሜን አቸፈር ወረዳ የግል ዘር አብዥ ድርጅት (እናጌት) እንዲሁም ከቡሬ ወረዳ በቀጥታ የዘር
ግብይት ስርዓት የተሳታፊ የዘር ብዜት ህብረት ሥራ ማህበር (ሰርተን እንደግ) የመስክ ምልከታው የተካሄደባቸው
ማህበራት ናቸው፡፡ በመስክ መልከታው ወቅት አግኝቼ ቃለ መጠይቅ ያደረጉላቸው አርሶ አደር በትሀ አስማረ እና
ይህዓለም ተሰራ እንዳሉት በመጀመሪያ ሲነገረን ሙሉ በሙሉ ለመቀበል ተቸግረው እንደነበር እና መንግስት ያመጣው
ይጠቅም እንደሆነ እንጂ አይጎዳም በማለት ለሁለት ቀን የተሰጠውን ስልጠና እንደወሰዱ እና ወደስራ እንደገቡ ጠቅሰው
ከቡቃየው ጊዜ ጀምሮ እስከ ፋሬው ድረስ ያለው ሄደት በጣም አስደሳች እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም ከመስክ ምልከታው የተገኙ ጠንካራና ደካማ ጐኖችን በማንሳት የተለያዩ ውይይቶችና የመፍትሄ
አቅጣጫዎችን ተሳታፊዎቸ አስቀምጠዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጂ
ዲን የሆኑት ዶ/ር ሰለሞን አዲሱ የመስክ ምልከታው አይን ከፋች እንዲሁም አስተማሪና አበርታች እንደነበር ገለፀው፤
ዩኒቨርሰቲው ከመማር ማስተማሩ ባለፈ የማህበረሰቡን ችግር የሚቀርፉ ምርምሮችን እያካሄደ እንደሚገኝ እና ለአርሶ
አደሮች እንዲሁም በዘር ዘርፍ ለሚሰሩ አካላት የረጅም እንዲሁም የአጭር ጊዜ ስልጠናዎች እንደሚሰጡ እና ከጐናቸው
በመቆም በጋራ እንደሚሰራ አሳስበዋል፡፡

The Ethiopian Maritime Academy brings together some of the most highly capable Ethiopian engineering graduates for a 6-month training program. The goal of the training is to provide trained and qualified man power for international maritime business operators.

The training provides cadets with a harmonious learning environment where they have access to all the necessary tools for becoming world-class seafarers.

The academy continued training and supply of highly competitive cadets which can positively impact international maritime business venture.

Accordingly, 104 cadets /officers in charge of an Engineering Watch and Electro-Technical officers) admitted to BDU' Maritime Academy before 6 months have effectively completed their training. The graduation is celebrated in the presence of Prof. Sarah Anyang, the African Union Commissioner for Human Resources, and Science and Technology, Dr. Baylie Damtie (President of the university), and representatives of EMTI.

BDU’s Institute of Disaster Risk Management and Food Security Studies has hosted the annual consultative meeting of Partners Enhancing Resilience for People Exposed to Risk (Periperi U) under the theme “A call to engage: Deepening Risk Knowledge –Advancing Resilience). In his introductory remark to the meeting Dr. Abrhamh Mebrat, director of the IDRMFSS, noted that the objective of hosting the annual consultative meeting is to share knowledge and experience on building disaster resilient community. The meeting would also be a beginning to work hand-in-hand to bring risk free and resilient Society, he added. Natural hazards and human-induced disasters are recurrent phenomenon in Africa causing loss of life and livelihoods, displacement of people, damages to public and infrastructures, and that it is by application of science and technology through education, research and outreach endeavors that we will reduce these problems, said BDU’s Vice-President for Research and Community Service Dr. Mulunesh Abebe in her opening speech. In this regard, Bahir Dar University has introduced Disaster Risk Management education to be equipped with all the scientific capabilities of forecasting and managing disaster and risks, she added. Her Excellency Prof. Sarah Anyang, the African Union Commissioner for Human Resources, and Science and Technology, different Periperi U partners, representatives from UN agencies, NGOs and Universities have attended the meeting. Finally, Prof. Sarah and her team have visited BDU and discussed with BDU’s President about the contribution of universities in general and Pan African Universities (run by African Union) in Particular in the development of Africa.

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቦርድ በ07/01/2010 ባደረገው ስብሰባ የዩኒቨርሲቲው መምህርና ተመራማሪ ለሆኑት ዶ/ር አለማየሁ ቢሻው አምስተኛውን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል፡፡ በመሆኑም የኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት በመላው የዩኒቨርሰቲው ማህበረሰብ ስም አምስተኛውን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ዕድገት ላገኙት ለፕሮፌሰር አለማየሁ ቢሻው “እንኳን ደስ አለዎት!” እያለ የደረጃ እድገቱ በዩኒቨርሰቲው እየተከናወነ ላለው ተቋማዊ ለውጥ ስኬት ፋና ወጊ በመሆኑ የተሰማውን ደስታ ለመግለጽ ይወዳል፡፡

ፕሮፌሰር አለማየሁ ቢሻው በትምህርት እና ስነ-ባህሪ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ ሲሆኑ ከመደበኛ ሥራቸው በተጨማሪ በኮሌጁ እና በዩኒቨርስቲው ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ የሚገኙ ምሁር ናቸው፡፡ በመሆኑም ከመማር ማስተማሩ ጐን ለጐን ከ32 በላይ ችግር ፈች የሆኑ የምርምር ሥራዎችን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ በሆኑ ጆርናሎች በማሳተም ለሀገርና ለወገናቸው አበርክተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ 13 ያልታተሙ ምርምሮችን እና 4 የፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ ስራዎችን ሰርተዋል፡፡

ፕሮፌሰር አለማየሁ ቢሻው ሌሎች ለዕድገቱ የሚጠየቁ መስፈርቶችን ከምርምር ሥራዎቻቸው ጎን ለጎን በተሰጣቸው ኃላፊነት ሁሉ በመግባት የድህርምረቃ ጥናት ዲን፣ የፕሬዘዳንት ጽ/ቤት ሃላፌ፣የባሕር ዳር ኢዱኬሽን ጆርናል ዋና ኢዲተር፣ የስርዓተ ትምህርት ፒኤችዲ ፕሮግራም መሪ፣ የፕላኒንግ ኦፊሰር፣ የርቀት ትምህርት አስተባባሪ፣ የተማሪዎች ዲን፣ የማህበረሰብ አገልግሎት አስተባባሪ በመሆን የሰሩ እና በሌሎች የተለያዩ የኮሚቴ ስራዎችም ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርገዋል፡፡

በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍም በሙያቸው በርካታ አገልግሎቶችን በመስጠት ሀገርና ወገን የሚጠቅም ሥራ እያበረከቱ ያሉ ምሁር መሆናቸውን በመገንዘብ ጭምር ነው የዩኒቨርሲቲው ቦርድ ሙሉ ኘሮፌሰርነት የማዕረግ እድገት የሰጣቸው፡፡

BDU and the University of Cape Town, South Africa have signed MoU to promote international cooperation and collaboration in the field of education in general and research in particular.

Both institutions have specifically agreed to work together on areas such as, encouraging faculty and student exchange, development of progression programs, developing short term courses and internships, joint research and development projects, organizing joint conference and workshops, Co-Publishing and launching of dual postgraduate programs.

The president and Vice presidents of Bahir Dar University have discussed with Finland Ambassador to Ethiopia H.E Helena Airaksinen and her team today at wisdom Tower to work together on different areas of collaborations. They have particularly discussed about the modality of delivering “Finland 100-women in Society and Development” seminar, which will be held in Bahir Dar on 10th and 11th of November 2017 as part of the celebration of 100 years of independence of Finland. 

BDU’s President Dr. Baylie Damtie has received “AFRICA VICE CHANCELLOR/PRESIDENT/ OF THE YEAR-2017” award from All Africa Students Union (AASU) during the 6th edition of the Union’s summit at the Cape Coast, Ghana from August 18-25, 2017.  The award is given in recognition of Dr. Baylie’s important role in promoting quality higher education in Ethiopia as well as for his immense support for students’ role in governance. The award has also take cognizant of Dr. Baylie’s quest for exceptional excellence and continual improvement within the higher education space in the continent.   All Africa Students Union is a Pan African Students organization formed to galvanize the young people particularly students into all the efforts geared towards the development of the African continent. It was established in 1972 and now has presence in all 55 countries, and has played among other, an important role in the struggle against colonialism and apartheid in Africa.  The union has been honoring personalities and institutions that have distinguished themselves in their areas of endeavor to uplift Africa from its current predicaments.   

Pages