Latest News

ትምህርት ክፍሉ ለመጀመሪ ጊዜ የሚያስመርቃቸው የ3ኛ ዲግሪ እጩ ተመራቂዎች ተቋቁሞ
*******************************************************************

በሙሉጎጃም አንዱዓለም
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሂዩማኒቲስ ፋኩልቲ በኢትዮጲያ ቋንቋዎችና ስነ-ፅሁፍ ትምህርት ክፍል የመጀመሪያ የሆነውን በ3ኛ ዲግሪ የመጨረሻውን የጥናታዊ ጽሁፍ ተቋቁሞ ሀሙስ የካቲት 14፣2011 ዓ.ም. በደመቀ ሁኔታ አካሄደ፡፡

የፋኩልቲው አንጋፋ መምህርና ተመራማሪ ዶ/ር ማረው ዓለሙ ፕሮግራሙን በንግግር ሲከፍቱ እንደተናገሩት አገር በቀል በሆነው የአማርኛ ቋንቋ በ3ኛ ዲግሪ ደረጃ መሰራቱ ዋና ዓላማው ቋንቋውን ለማሳደግና ትምህርቱን ለማስፋፋት እንዲሁም የጥናት ዉጤቱ ለተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ግብዓት ለማድረግ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ዶ/ር ማረው አክለውም እርሳቸው በሚመሩት አማርኛን ማስተማር የ3ኛ ዲግሪ ፕሮግራም የሚጻፉ ጥናታዊ ጹህፎች ደረጃቸውንና ጥራታቸውን የጠበቁ ሆነው እንዲቀጥሉ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጡ ተናግረዋል፡፡

የፋኩልቲው ዲን ዶ/ር ዳዊት አሞኘም ለተመዘገበው ስኬት በሂደቱ ውስጥ የተሳተፉትን ሁሉንም በፋኩልቲው ስም አመስግነው የእለቱን አቅራቢ እንኳን ደስ አለህ በማለት በሶስት አመት ከመንፈቅ በሆነ ጊዜ ብቻ ፕሮግራሙን ለማጠናቀቅ መቻሉ በራሱ ትልቅ ስኬት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ምናልባትም በዚህ አጭር ጊዜ ሲጠናቀቅ በዩኒቨርሲቲው ታሪክ የመጀመሪያው ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

የአሁኑ እጩ ተመራቂዎች በፋኩልቲው ስር የኢትዮጲያ ቋንቋዎችና ስነ-ፅሁፍ መምህር የሆኑት አቶ ማስተዋል ውበቱ እና የዓርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት አቶ ሐይላኣይ ተስፋይ ሲሆኑ በዕለቱ ጥናታቸውን ያቀረቡት አቶ ማስተዋል የጥናታቸው ርዕስ “ የትብብር ብልሀታዊ ማንበብ ዘዴ” የተሰኘ ነው፡፡ ለጥናቱ መነሻ የሆነው ከ1-8 ክፍል ያሉ ተማሪዎች የማንበብ ልምዳቸውና ተነሳሽነታቸው አናሳ መሆኑንን የሚጠቁሙ ጥናቶች መኖራቸው እና የ1ለ5 የትብብር ብልሀትም በአግባቡ አለመተግበሩ እንደሆነ አቅራቢው ጠቁመው ጥናታቸውም የተጠቀሰውን የንባብ ብልሀት ለመፈተሸ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

እጩ ተመራቂው ስለ ስለጥናታቸው ለሰላሳ ደቂቃ ያህል ካቀረቡ በኋላ ከውጭ እና ከውስጥ ለመጡ ገምጋሚዎች እንዲሁም ከታዳሚው ለተነሱ አጠቃላይ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በመጨረሻም የእለቱ ሊቀመንበር የክፍቱ ተቋቁሞ እንደተጠናቀቀ ገልጸው ተቋቁሞው ከ15 ደቂቃ ረፍት በኋላ በዝግ እንደሚቀጥል በማመልከት ለነበረው ጊዜ ታዳሚውን አመስግነዋል፡፡

              በትዕግስት ዳዊት

የተቀናጀ የዘር ሴክተር ልማት በኢትዮጵያ/ ISSD/ የግምገማ እና የልምድ ልውውጥ አውደ ጥናቱን ከየካቲት 11፣ 2011 ዓ.ም. ጀምሮ በባህር ዳር አካሄደ፡፡

 

ዶ/ር ደረጀ አያሌው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ መምህርና የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮጀክት ሳይንቲፊክ አስተባባሪ (ISSD Project Amhara Unit Scientific Coordinator) በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ እንዳሉት የአውደ ጥናቱ ዋና አላማ በአመቱ የተሰሩ ስራዎችን ለመገምገምና ስራዎችን ለማስቀጠል ነው ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ለስኬታማ አፈፃፀም ምን መደረግ እንዳለበት ለመምከር እንዲሁም በተመዘገቡት ስኬታማ ተሞክሮዎች ዙሪያ የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ታስቦ የሚካሄድ  አውደ ጥናት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

 

አክለውም የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮጀክት ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በተጨማሪ በ5 ቦታዎች ማለትም ከኦሮሚያ ዘር ኢንተርፕራይዝ ፣ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣ ፣ ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ እና ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመሆን እየሰራ ያለ ፕሮጀክት እንደሆነ ገልፀው ሁሉም የፕሮጀክቱ ሰራተኞች በየአመቱ አንድ ቦታ ላይ በመሰባሰብ የተሰሩ ስራዎችን በመገምገም የልምድ ልውውጥ የሚያደርጉበትና ችግሮችን በማረሞ በቀጣይ የዘር ሴክተሩን ለማሳደግ የሚሰራበት ነው ብለዋል።

 

የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት ፕሮጀክት ጥሬ ገንዘብን በቀጥታ ለአጋር አካላት የማይሰጥ ይልቁንም አርሶ አደሮችን በማደራጀት የተለያዩ ስልጠናዎችን በመስጠት መሬታቸውን ክላስተር በማድረግ ክህሎትና አመለካከት በማምጣት  ደረጃውን የጠበቀ ዘር ማምረት እንዲቻል ስራ እንደሚሰራ ጠቁመዋል። በተጨማሪም እንደ አስተባባሪው ገለፃ ፕሮጀክቱ የድህረ ምርት ብክነትን ለመቀነስ ስልጠና ይሰጣል ብለዋል።

 

ዶ/ር ደረጀ እንዳሉት ፕሮጀክቱ በዋናነት ጥራት ያለው፣ አርሶ አደሩ የመረጠውና በምርምር የተገኘ ዘርን ወቅቱን ጠብቆ በተፈለገው መጠን ለአርሶ አደሩ እንዲደርስና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘዬ ለመቀየርና ኢኮኖሚን ለማሳደግ አልሞ ይሰራል ብለዋል። የልምድ ልውውጡም የት ላይ እንዳሉ፣ ሌሎቹ  ምን የተሻለ ስራ እንደሰሩ የሚታይበት እና ለተሸለ ስራ ስንቅ የሚሰነቅበት እንደሆነ ዶ/ር ደረጀ ተናግረዋል። እነዚህን መልካም ተሞክሮዎችን ስንወስድ በመላ ሀገሪቱ ሊኖር የሚችለው የዘር ጥራት ዝውውር ያደርጋል ብለዋል።

 

ዶ/ር ደረጀ ዘር ላይ መስራት ውጤታማ ስለሚያደርግ አርሶ አደሮች ያመረቱትን ምርት ለገበያ እንዲያደርሱ ያግዝ ዘንድ የተለያዩ የዘር ማበጠሪያ ማሽኖች በተለያየ ጊዜ ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመተባበር ተገዝተው ለአምራች ገበሬው ተሰጥቷል። ይሁን እንጂ ማሽኖቹ በኤሌክትሪክ እጦት ምክንያት አገልግሎት ላይ እንዳልዋሉ ጠቁመዋል። አርሶ አደሮች እንዲቀየሩና እንዲስተካከሉ ግብርናንም ለማሳደግና ለማዘመን ማሽኖቹ አገልግሎት እንዲሰጡ ያለባቸው የኤሌክትሪክ ችግር እንዲቀረፍ ጥሪ አቅርበዋል።

 

ዶ/ር አምሳሉ አያና የISSD ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስኪያጅ እንዳሉት የዘር ስርዓቱን ለማሻሻል የዘር እሴት ሰንሰለቱ ቀልጣፋ መሆን አለበት ብለው  ከዝርያ መረጣ ጀምሮ ያለውን ሰንሰለት በመቀነስ ብሎም ቀልጣፋ በማድረግ ምርትና ምርታማነትን ለማምጣት እንዲቻል እየተሰራ ነው ባለዋል፡፡ ለዚህ ውጤታማነት ከነሀሴ 2001 ዓ/ም ጀምሮ ከአራት ክልሎች ጋር ISSD በቅንጅት በመስራት ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡

 

This public lecture is part of the lecture series Perspectives on Positive Peace entitled as ‘Data Driven Democracy – How platforms provide opportunities for participation, community organizing, public engagement and business development’ was undertaken by The Department of Political Science and International Studies of Social Sciences Faculty, Bahir Dar University in collaboration with the Friedrich-Ebert-Stiftung.

 

The head of the Department of Political Science and International Studies, Mr Gebretsadik Awgichew, in his welcoming speech, said that the major objective of the gathering is to talk about the potentials of data for democratic systems. Data driven forms of civic participation increasingly become the modern approach to engage with citizens. Civic participation is considered a cornerstone of democracy. This form of data-driven democracy and civic participation promotes an understanding of democratization processes and democratic systems.

 

Mr. Gebeyehu Mengesha, the Vice Dean for Postgraduate, Research and Community Service of Social Science Faculty, in his opening remarks, said that Relevant data is used to create strong strategies, policies, programs and future plans which will be realistic. He added data can be used for performance evaluation, monitoring, controlling and auditing for institutions and organizations which are very important for democratic value creation and for suggesting new ways of doing things.

 

The speaker Mr Henrik Flor focused on the importance of data in the formation of a system that functions healthily and strong. He said obtaining data is a powerful tool for transparency and accountability of a certain functioning system, be it a state or an organization. Underscoring the indispensable role of data, the speaker argues that truthful data can help in bringing local and national democracy and in realizing proper utilization of public finance and budgeting. Moreover, such data can also play a pivotal role in process of policy making.

 

Mr Flor concludes that the future of our modern world depends on the timely and effective use of data. He reminds the scholarly community once again to be sensitive in building their claims with relevant and suffice data implicating the otherwise use might not serve the demand of the modern era.

 

 

BDU STEM Center Started the 4th STEM-Girls Camp Program

The Bahir Dar University STEM Center started its STEM-Girls camp program which is running from February 3 to 10, 2019. The training was officially opened by Dr Zewdu Emiru, the Vice President for Information and Strategic Communications of the University. The training is taking place in the Peda campus where dormitories and training facilities for the program are provided. 73 female students from grades 9 to 12 of all public and private high schools found in Bahir Dar City are attending the training. It is managed by 15 teaching staff pooled from all STEM departments of the university. The training includes STEM lab practices, life skill, team-work, field exercises, games with funny approaches of science, site visits related to STEM, a visit to Bahir Dar Maritime Academy and Bahir Dar University College of agriculture and environmental sciences (Nursery site, animal farm …). The STEM-Girls camp is an annual program of the BDU STEM center conducted during the semester break of schools. This year camping program is as usual is prepared in a competition form. Four Groups are competing and they are named after the well-known Ethiopian female scientists Prof Yalemtsehay Mekonnen, Prof Sosina M. Haile, Dr Segenet Kelemu and Dr Debrework Zewdie. The grouping is to inspire our future female scientists to follow the tracks of their fellow female senior professors. The camp will have competition throughout the whole week and finally the winner group will receive the winners’ cup at the end of the weeklong program.

 

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ተስፋ የህፃናትና አረጋዊያን መርጃ ማእከልን ጎበኙ!!
 

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ተማሪዎች በተስፋ የማህበረሰብ አቀፍ ልማት ማህበር ማዕከል ጥር 25 በመገኘት የማዕከሉን የስራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው በመጎብኘት ለማህበሩም የተለያዩ ድጋፎችን አድርገዋል። በጉብኝቱም የማዕከሉን ሥራ አድንቀዋል፡፡

በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ድህረ ምረቃ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ዲን የሆኑት ዶ/ር ተከተል አብርሃም በዕለቱ ተገኝተው ከመምህራን፤ ከሰራተኞችና ከተማሪዎች ያሰባሰቡትን ጥሬ ገንዘብ እና የተለያዩ አልባሳት የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ  ተወካይ በተገኙበት ለማህበሩ ስራ አስኪያጅ ለአቶ ስለሽ ጌታቸው አስረክበዋል፡፡

ማህበሩ በ2000 ዓ.ም. ኪዳነ ምህረትና ባታ በተሰኙ እድሮች በ27 አባላት መነሻነት የተቋቋመ ሲሆን ባሁኑ ስዓት 100 ህፃናትን  የማስተማርና የምግብ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ከሁለት ሺ በላይ ለሚሆኑ እና ዕድሚያቸው ከ5 ዓመት በላይ ሆነው በደማቸው ኤች.አይ.ቪ ያለባቸውን የማህበረሰብ ክፍሎች ቤት ለቤት በመሄድ ድጋፍ እንደሚሰጥ የማዕከሉ ኃላፊ በዕለቱ ገልጸዋል፡፡

 አቶ ስለሽ ጌታቸው አክለውም  ማህበሩ አገር በቀል እንደመሆኑም ከማህበሩ አባላት መዋጮ ባሻገር የተለያዩ የገቢ ማስገኛ ፕሮግራሞችን የሚያካሂድ እንደሆነ ገልጸው ለታደሙትም የማህበሩ አባል በመሆን  የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡

በሙሉጉጃም አንዱዓለም

በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ብሉ ናይል ውሃ ኢንስቲትዩት ስር የሚገኘው ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ መንደር መመስረት (Climate Smart Villages/CSV/) የተሰኘው ፕሮጀክት በገጠር ልማት ላይ ለመስራት ስምምነቱን በዩኒቨርሲቲው ጥበብ ህንፃ አዳራሽ አሳወቀ፡፡

የመክፈቻ ንግግሩን ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር ዶ/ር የሻንበል መኩሪያው ሲሆኑ ፕሮጀክቱ ሊሰራ ያሰበው አኩሪ ተግባር በመሆኑ በወረቀት ላይ ያለው ተግባራዊ ሆኖ እንዲታይ አሳስበዋል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ ፕሮጀክቱ ከተለያዩ አካባቢዎች የሰበሰባቸውን ተሞክሮዎች ያካተቱ የተለያዩ ፅሁፎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተካሂዷል፡፡ የታለመው ንድፈ ሀሳብ ወደ ተግባር ተለውጦ ይታይ ዘንድ ከዩኒቨርሲቲው የበላይ አመራሮች ጀምሮ ሁሉም የሚመለከተው አካል ርብርብ ማድረግ እንደሚገው የፕሮጀክቱ ባለቤቶችና በሙያው የተካኑ ምሁራን ተናግረዋል፡፡

በእለቱም የወደፊት የትኩረት አቅጣጫዎች ከተለዩ በኋላ ተግባራዊ እንቅስቃሴውንም ተጨባጭ ለማድረግ የስራ ድርሻ ክፍፍል ተደርጓል፡፡

BDU signs Memorandum of Understanding with icepe, International Center for Insect Physiology and Ecology.
The occasion is held at the president's office with the presence of icipe delegates and University's officials. The signatories were the president of Bahir Dar University, Dr Firew Tegegne and Director General of icipe, Dr Segenet Kelemu.

In the ceremony, the distinguished scientist Dr Segenet Kelemu, Director of icipe, shared her experience about the importance of focusing on one thing and stand out in it to be a successful professional or an organization leader. She also underscored that it is always right to work hard on what one has and strive towards something great. Explaining her the remark, she said one cannot or shall not stay without a car while having a car is very important, but, for example, begin with a Volkswagen, and then steadily works hard to have a dream Mercedes car.

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበበ ጊዎን ሆስፒታል ያሰለጠናቸውን ስፔሻሊስት ሐኪሞች በክልሉ የተለያየ ሆስፒታሎች የማህበረሰብ አገልግሎት እንዲሰጡ አሰማራ፡፡

ለአንድ አመት የሚቆየው ይህ የሐኪሞች ስምሪት በክልሉ በተለይም በባሕር ዳር አካባቢ በጥበበ ጊዎንና በፈለገ ሕይወት ሆስፒታሎች ያለውን የስራ ጫና ለመቀነስና ታካሚዎችም ርቀው ሳይጓዙ በአቅራቢያቸው አገልግሎቱን እንዲያገኙ የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

የጥበበ ጊዎን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋና ተቀዳሚ ዳይሬክተር ፐሮፌሰር የሺጌታ ገላው ከመጋቢት 2009 ዓ.ም ጀምሮ ሃኪሞችን ወደ ተለያዩ ሆስፒታሎች የመላክ ተሞክሮ እንደነበረ ገልጠው ወደፊትም ይህን ስራ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ቃል ገብተዋል፡፡ 
በዚህ ዙር 13 የሚደርሱ ስፔሻሊስት ሐኪሞች የተሰማሩ ሲሆን ስድስት የጠቅላላ ቀዶ ሕክምና እና ሰባት የማህጸንና ጽንስ ስፔሻሊስት ሓኪሞች መሆናቸው ተገልጧል፡፡ እነዚህም ሐኪሞች ከክልሉ ጤና ቢሮ ጋር በመነጋገር የበለጠ አገልግሎት ወደሚሰጡበት ምዕ/ጎጃም፣ ምስ/ጎጃም፣ ደቡብ ጎንደር፣ ሰሜን ሸዋና አዊ ዞኖች የተመደቡ ናቸው፡፡

በስነስርዓቱ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የጤና ቢሮ ተወካይ አቶ አበበ ከህክምናውም ባሻገር ጥሩ የአሰራር ስርዓት በመዘርጋት በቆይታቸው ለውጥ እንዲያመጡ አደራ ብለዋል፡፡

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘም ለሃኪሞቹ ባስተላለፉት መልዕክት የሙያውን ክብር በመጠበቅ ማህበረሰባችን የሚጠብቀውን የህክምና አገልግሎት ከመልካም ሙያዊ ስነ ምግባር ጋር በማጣመር አርዓያነት ያለው ተግባር ፈጽመው በመመለስ የራሳቸውንም ሆነ የተቋማቸውን ስም በበጎ እንዲያስጠሩ በማሳሰብ የግል ተሞክሯቸውንም ለታዳሚው አጋርተዋል፡፡ የተለያዩ እንግዶች ምስጉን ሐኪሞችና የሐኪሞቹ አሰልጣኝ መምህራን በተገኙበት ስነ-ስርአት ላይ ከሐኪሞቹም የተለያዩ ሃሳቦች የተነሱ ሲሆን በመጨረሻም ፕሬዚደንቱ የማስታወሻ ስጦታ ለተጓዥ ሀኪሞች አበርክተዋል፡፡

በኢትዮ- ሱዳን ህገ-ወጥ ፍልሰትን ለመከላከል ምክክር ተካሄደ

==================================

በኢትዮጵያና በሱዳን ድንበር መካከል የሚስተዋለውን ህገ-ወጥ የሰዎች ፍልሰት ህግን የተከተለ  እንዲሆን ለማድረግ በሁለቱ አጎራባች ሀገራት ሙሁራንና የሚመለከታቸው አካላት መካከል Better Migration Management Sudan/ Ethiopia በሚል መሪ ቃል በባህር ዳር ምክክር ተካሂዷል፡፡

በምክክር መድረኩ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የገዳሪፍ ግዛት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ፕሮፌሰር ኢብራሂም የሱፍ ለዘመናት የዘለቀውን የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች ሰላማዊ ግንኙነት በሚያጠናክር መልኩ ፍልሰቱን ህጋዊ ለማድረግ የተጀመረው ፕሮጀክት አሁን ያለበት ደረጃ በመድረሱ የተሰማቸውን  ላቅ ያለ ደስታ ገልፀዋል፡፡

ፕሮፌሰር ኢብራሂም አክለውም የገዳሪፍ ግዛት ዩኒቨርሲቲ የምርምር ተቋም በመሆኑ  በማህበረሰብ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ ትኩረት ሰጥቶ  እየሰራ እንደሚገኝ አትተው ዩኒቨርሲቲአቸው   በኢትዮጵያ ከሚገኙ የድንበር አዋሳኝ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በሰዎች ፍልሰት ዙሪያ በጥምረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ በበኩላቸው  በምክክር መድረኩ ለተገኙ ተሳታፊዎች እና ባለ ድርሻ አካላት  እንኳን ወደ ባህር ዳር መጣችሁ ካሉ በኋላ ስለፍልሰት የሚካሄደው ምክክር በሰው ልጅ መገኛ በሆነችው ሀገር መሆኑ  ውይይቱን ታሪካዊ ያደርገዋል ብለዋል፡፡ አክለውም ፍልሰት ለሰው ልጅ ቀድሞ የነበረ እና ወደፊትም የሚኖር ተፈጥሯዊ ጉዳይ እንደሆነ ገልፀው ነገር ግን ህጋዊ መልክ የያዘ እና የዜጎችን ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ባከበረ መንገድ መከናወን ይገባዋል ብለዋል፡፡

ፍልሰት በህጋዊ ይዞታ እንዲኖረው ለማድረግ የምርምር ማዕከል ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዚደንቱ የገንዘብ ድጋፍ እያደረጉ ያሉትን የጀርመን ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት እና የአውሮፓ ህብረት አመስግነዋል፡፡

በምክክር መድረኩ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከገዳሪፍ ግዛት ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጋር በጋራ ያዘጋጁት ጥናታዊ ጽሁፍ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡ በውይይቱም ከሁለቱም ሀገራት የተውጣጡ ተማሪዎች፣ ተመራማሪዎች፣ የመንግስት አስፈፃሚ አካላት፣ አርሶ አደሮች እና ወደ ገዳሪፍ ለስራ የሚሄዱ ኢትዮጽያዊያን ሰራተኞች ተገኝተዋል፡፡

በትዕግስት ዳዊት

 

Bahir Dar University has signed an agreement with Lucy Academy to launch E-learning programs. The partnership agreement is believed to promote access to quality education in Africa and beyond.

 

For more information about the E-learning programs visit https://www.lucyacademy.com/

 

Learn anytime, anywhere!

 

Pages