ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ብዝኃ-ሕይወት ኢንስቲትዩት ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ

29 Oct, 2025


በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና በኢትዮጵያ ብዝኃ-ሕይወት ኢንስቲትዩት መካከል በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም ተፈራረሙ ፡፡

የመግባቢያ ሰነዱ ዋና አላማ በኢትዮጵያ ብዝኃ-ሕይወት ኢንስቲትዩት እና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መካከል የሥራ ግንኙነት መፍጠር ሲሆን ተዋዋይ ወገኖች የጋራ ፍላጎቶችን፣ መርኃ-ግብሮችን እና ተግባራትን በጋራ ለማቀድና ለመተግበር ይችሉ ዘንድ መረጃ እንዲለዋወጡ ማገዝ ነው ።

ይህ የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ አስገዳጅ ያልሆነ፣ ነገር ግን መደበኛ የሆነ የጋራ ስልታዊ ጠቀሜታ ባላቸው መስኮች በጋራ ለመሥራት በተለይም በዓለም አቀፍ የብዝኃ-ሕይወት ስምምነቶች እና በብሔራዊ ልማት ዕቅዶች ውስጥ ኢትዮጵያ ለገባችው ቃል ኪዳን አስተዋፅዖ ለማድረግ ያላቸውን ፍላጎት ያሳያል።

የመግባቢያ ሰነዱ ለአምስት ዓመት የሚቆይ ሲሆን እንደ ውጤታማነቱ ታይቶ ሊታደስ እንደሚችል ከውይይቱ መረዳት ተችሏል፡፡

imageimageimage