Event Grid-2 Column
Lorem ipsum dolor sit amet, consectetur adipiscing elit, sed do eiusmod tempor incididunt ut labore et dolore magna aliqua.
01 October, 2025
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ "ሠላም አካዳሚ" የማህበረሰብ ትምህርት ቤት በይፋ አስጀመረ
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ "ሠላም አካዳሚ" የማህበረሰብ ትምህርት ቤት በይፋ አስጀመረ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ - (መስከረም 20 ቀን 2018ዓ/ም)የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎት አካል የሆነው "ሠላም አካዳሚ" የተሰኘው የማህበረሰብ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ተቀብሎ ሥራ መጀመሩን አስታወቀ። አካዳሚው የዩኒቨርሲቲውን ሠራተኞች ለመደገፍና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ያለመ ነው።
ከዚህ ቀደም በ2017 ዓ.ም. የቅድመ መደበኛ (KG 1 እስከ KG 3) ትምህርትን ሲሰጥ የቆየው ሠላም አካዳሚ፣ በዚህ ዓመት ደግሞ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን በመቀበል ሙሉ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መስጠት ጀምሯል። ይህ መስፋፋት የዩኒቨርሲቲው ለሠራተኞቹ ከሚሰጣቸው የማህበረሰብ አገልግሎቶች መካከል ዋነኛው ሲሆን፣ በተለይም የሠራተኞችን ከኑሮ ውድነት አንጻር ያለውን ጫና በማቅለል ረገድ ትልቅ ድጋፍ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
30 September, 2025
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከክልሉ መንግሥት የዋንጫ ሽልማት ተበረከተለት
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከክልሉ መንግሥት የዋንጫ ሽልማት ተበረከተለት
መስከረም 19/2018 ዓ/ም (ባሕር ዳር): ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ/ም የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ብሔራዊ ፈተና ያስፈተናቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (100%) በማሳለፉ ከአማራ ክልል መንግሥት የላቀ የዋንጫ ሽልማት ተበረከተለት።
ይህ ክብር የተጎናጸፈው በተለይ የዩኒቨርሲቲው ስቲም (STEM) ማዕከል ባስመዘገበው አስደናቂ ውጤት ነው።
የሽልማት ሥነ-ሥርዓቱ ዛሬ መስከረም 19/2018 ዓ/ም በባሕር ዳር ከተማ የተካሄደ ሲሆን፣ የዋንጫ ሽልማቱን ለዩኒቨርሲቲው ያስረከቡት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር አብዱ ሁሴን ናቸው።
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስቲም ማዕከል ለብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው 41 ተማሪዎች ውስጥ፣ ሁሉም ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባቸውን ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገብ 100% የማለፍ ውጤት አስመዝግበዋል።
25 September, 2025
በአፍላቶክሲን ብክለት ላይ የሚደረገውን ትግል የሚያግዝ ተስፋ ሰጪ አዲስ መሣሪያ በባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተመራማሪዎች ይፋ ተደረገ
በአፍላቶክሲን ብክለት ላይ የሚደረገውን ትግል የሚያግዝ ተስፋ ሰጪ አዲስ መሣሪያ በባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተመራማሪዎች ይፋ ተደረገ
(መስከረም 15/2018ዓ.ም ISC/BiT) በአፍላቶክሲን ብክለት ላይ የሚደረገውን ትግል የሚያግዝ ተስፋ ሰጪ አዲስ መሣሪያ በባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተመራማሪዎች ፣ ዊዝደም ኢንተርፕራይዝ ከ Stichting Wageningen Research (SWR) Ethiopia's RAISE-FS project ባገኘው የኢኖቬሸን ፈንድ ድጋፍ ታግዞ ይፋ ተደርጎ በዛሬው ዕለት ለአውደ ርዕይ ቀርቧል። ይህ አዲስ ፈጠራ፣ ቀላል፣ ወጪ ቆጣቢ የሆነው የእርጥበት መለኪያ ኪት፣ የደረቁ ምግቦችንና መኖ ምርቶችን ከብክለት ለመከላከል ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
17 September, 2025
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አሳታሚ ድርጅት አቋቋመ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አሳታሚ ድርጅት አቋቋመ
የመጀመሪያ ሥራው የአፄ ዘርአ ያዕቆብ ዜና መዋዕል ሆነ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መጻሕፍትን በማዘጋጀትና በማሳተም ለማሰራጨት የሚያስችለውን “ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ” የተሰኘ አሳታሚ ድርጅት ማቋቋሙን አስታወቀ። ፕሬሱ የመጀመሪያ ሥራው አድርጎ “የዐፄ ዘርአ ያዕቆብ ዜና መዋዕል (1426 - 1460 ዓ.ም) ግእዝ-አማርኛ ትርጉም እና ሐተታ” የተሰኘ መጽሐፍ አሳትሞ ለገበያ አብቅቷል።
ይህ መጽሐፍ ከግእዝ ወደ አማርኛ የተተረጎመ ሲሆን፣ የመካከለኛውን ዘመን ታላቁን ንጉሥ አፄ ዘርአ ያዕቆብ የዘመን ታሪክና የእለት ከዕለት እንቅስቃሴ በዝርዝር ያቀርባል። 157 ገጾችን የያዘው ይህ ታሪካዊ ሰነድ፣ በመካከለኛው ዘመን የኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ለሚደረጉ ጥናቶች ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተገልጿል።
መጽሐፉ በአሁኑ ጊዜ በባሕር ዳር ከተማ በሚገኙ የመጻሕፍት መደብሮች በ350 ብር እየተሸጠ ሲሆን፣ በቅርቡ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በደማቅ ሥነ ሥርዓት የሚመረቅ ይሆናል።
15 September, 2025
Israeli Medical Team Provides Advanced Training at Tibebe Ghion Specialized Hospital
Israeli Medical Team Provides Advanced Training at Tibebe Ghion Specialized Hospital
=================================================================
Bahir Dar, Ethiopia – September 14, 2025: A team of distinguished Israeli doctors, led by Prof. Elhanan Bar-On, a Pediatric Orthopedist, and Prof. Tzipora Strauss, a Neonatologist, has provided advanced training and clinical services at Tibebe Ghion Specialized Hospital, Bahir Dar University.