ድጋፍ ተበረከተ

                     ከግብረ ሰናይ ድርጅቶች የህክምና መሳሪያዎች ድጋፍ ተበረከተ       
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ስር ለሚገኘው የጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለአይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ጥገና ህክምና የሚውሉ መሳሪያን ጨምሮ ለዩኒቨርሲቲው ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አገልግሎት የሚሰጡ ልዩ ልዩ የህክምና ዕቃዎች ህንድ አገር ከሚገኘው ኦፕሬሽን አይ ሳይት ከተባለ የበጎ አድራጎት ድርጅት በርዳታ ተበርክቷል፡፡ከዚህ በተጨማሪ የበጎ አድራጎት ድርጅቱ ለመማር ማስተማር የሚውሉ ልዩ ልዩ መሳሪያዎች ለግሷል፡፡  

ዩኒቨርሲቲውም በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አማካኝነት የዩኒቨርሲቲውን የሚወክሉ ልዩ ልዩ የስጦታ እቃዎች ለበጎ አድራጎት ድርጅት ተወካዮች በምስጋና ስም አበርክተዋል፡፡