የፊልምና ትያትር ካሪኩለም

የፊልምና ትያትር ካሪኩለም ወርክሾፕ ተካሄደ
=========================
በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሂዩማኒቲስ ፋኩሊቲ የፊልምና ትያትር የስርአተ ትምህርት ቀረጻው ተጠናቆ የአስፈላጊነት ግምገማ ተደርጎበታል። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተጋበዙ የዘርፉ ባለሙያዎች ባቀረቡት የመነሻ ሃሳብ መስረት በታዳሚዎች ውይይት ተደርጎበታል።ዘርፉ ለአካባቢው እጅግ አስፈላጊ መሆኑ በውይይቱ በአትኩሮት የተነሳ ነጥብ ነው። በውይይቱ የዩኒቨርሲቲው ሰራትኞችና ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን ከክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የመጡ ባልሙያዎችም ተሳትፈዋል።