የጥበቃና ደህንነት ሰራተኞች ስልጠና

ለዩኒቨርሲቲው የጥበቃና ደህንነት ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ

***************************************

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስር ዳይሬክቶሬት እና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መምህራን አዘጋጂነት ለባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጥበቃና ደህንነት ሰራተኞች በፈጣን የላፕቶፕ ባለቤትነት ማረጋገጫ ስርዓት(Fast digital verification system in Laptop’s ownership) ዙሪያ በስነ-ምድርና መረጃ ቴክኖሎጂ ማዕከል የስልጠና አዳራሽ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መምህር የሆኑትና ስልጠናዉን የሰጡት  አቶ ሀብታሙ አለማየሁ ለሰልጣኞች በስልጠናው አስፈላጊነት ዙሪያ ገለፃ አድርገዋል፡፡ ይህ ቴክኖሎጂ የመረጃ አያያዝን እንደሚያዘምን፤ ጊዜና ጉልበትን እንደሚቆጥብ፤ ደህንነቱ የተረጋገጠ ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችል፤ የመረጃ መጥፋትን፤ በወረቀቶች መቀደድና መጥፋት ምክንያት የሚደርስ የአገልግሎት ችግርን እንደሚቀርፍ አቶ ሀብታሙ ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪም ይህ ቴክኖሎጂ ተአማኒ፣ ቀላልና ፈጣን በመሆኑ ለአጠቃቀም ምቹ እንደሆነ አቶ ሀብታሙ አለማየሁ ተናግረዋል፡፡

ፈጣን የባለቤትነት መለያ ስርዓት (Fast digital verification system customer’s property) የተሰኘዉ ይህ ቴክኖሎጂ በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች እንደሚሰራ የገለፁት አሰልጣኙ እነሱም የመረጃ ምዝገባ ስርዓት (QR Code Generator) እና የመረጃ ማረጋገጥ ስርዓት (Android Application) ይሰኛሉ ብለዋል፡፡

የስልጠናው ተሳታፊዎችም ስልጠናዉ አጭርና ግልፅ መሆኑን ገልፀው መሰል ስልጠናዎች በየጊዜው መዘጋጀታቸው የሰራተኛውን አቅም ያሳድጋል ብለዋል፡፡ ስልጠናዉ የተሰጠዉ ለአንድ ቀን ሲሆን 30 የጥበቃና ደህንነት ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡