የብሔራዊ ውይይት ተስፋዎች እና ፈተናዎች

በመጪው ብሔራዊ ውይይት ተስፋዎች እና ፈተናዎች ላይ ውይይት ተደረገ

የባሕር ዳር  ዩኒቨርሲቲ ማህበራዊ ሳይንስ ፋኩልቲ ከFRIEDRICH EBERT STIFTUNG ጋር በመተባበር ‹‹መጪው  ብሔራዊ ውይይት  ተስፋዎች እና ፈተናዎች››  በሚል ጭብጥ  የግማሽ ቀን አውደ-ጥናት በዋናው ግቢ የመሰብሰቢያ አዳራሽ አካሄደ፡፡  

 

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር እሰይ ከበደ በመክፈቻ ንግግራቸው ባለፉት አስርት ዓመታት እንደ ህዝብ በብዙ ችግሮች ያለፍን እንደሆነ በመገንዘብ ለነዚህ ችግሮች ምንጭ የሆኑትን በመለየት ምሁራኑ ችግሮችን እንድናልፋቸው ዘንድ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ ብዝሃነታችን አዙሮ በመጠቀም በመካከላችን መከፋፈል፣ መጠላላት፣ መገዳደል እንዲኖር የሚሰሩ ኃይላት እንደመሮራቸው ችግሮች እንዳይከሰቱ በትጋት መስራት ይገባል ብለዋል ዶ/ር እሰይ ከበደ፡፡

 

በሴሚናሩ Ethiopians Identity Crisis: Way Forward For the National Dialogue በፕሮፌሰር  ባህሩ ዘውዴ ፣ The Politics and Practices of Adjudicative and Deliberative Institution in Ethiopia: Lessons from Recent History በዶ/ር ተካልኝ ወልደማሪያም፣ Do No Harm: Managing Expectation in National Dialogue በፕሮፌሰር ሹመት ሲሻኝ፣ The Conflict in Northern Ethiopia and Its Ramifications በዶ/ር ቴዎድሮስ ሃይለማሪያም የተሰኙ ጥናታዊ  ፅሁፎች  ቀርበው  ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

 

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ማህበራዊ ሳይንስ ፋኩልቲ ዲን ዶ/ር ታዬ ደምሴ በበኩላቸው የዚህ አይነት ውይይት ቀጣይነት ያለው መሆኑን ጠቁመው የጥናታዊ  ፅሁፎች  አቅራቢዎችን እና ለዝግጅቱ መሳካት አስተዋፆ ያደረጉ አካላትን አመስግነዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ ክብርት አምባሳደር ዶ/ር የሽመብራት መርሻን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው  ከፍተኛ አመራሮች፤ የትምህርት ክፍሉ መምህራንና ተማሪዎች እንዲሁም ጥሪ  የተደረገላቸው ከተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የተውጣጡ ምሁራን እና ጥናት አቅራቢዎች ተሳትፈዋል፡፡

ዘጋቢ፡- ወንዳለ ድረስ