የስፔስ ሳይንስ ስልጠና መስጠት ተጀመረ
ለባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስቴም ማዕከል እና ለ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የስፔስ ሳይንስ ስልጠና መስጠት ተጀመረ
*********************************************************************************
(ሀምሌ 18/2014 ዓ.ም፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-BDU) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕ ጽ/ቤት ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ማህበረሰብ እና ዋሸራ ጂኦስፔስ እና ራዳር ሳይንስ የምርምር ማዕከል ጋር በመተባበር ባሕር ዳር ከተማ ከሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ትምርት ቤቶች የተውጣጡ እና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስቴም ማዕከል ተማሪዎችን ጨምሮ በስነ-ፈለግ ጥናት፣ እና በሳተላይት ቴክኖሎጂ ከሐምሌ 18-23/2014 ዓ.ም ለስድት ተከታታይ ቀናት የቆየ የክረምት ወቅት ስልጠና በዋናው ግቢ የቀድሞው ሴኔት አዳራሽ መስጠት ጀመረ፡፡
ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት በሳይንስ ኮሌጅ የፊዚክስ ትምህርት ክፍል ሀላፊ የሆኑት ዶ/ር ተስፋዬ ዳኜ እንዳሉት የስፔስ ሳይንስ ስልጠና ለልጆቹ መስጠታችን ተማሪዎች የወደፊት የትምህርት ዝንባሌያቸው ስፔስ ሳይንስ ላይ እንዲያተኩሩና ለሀገር ጠቃሚ ዜጋ ሆነው እንዲወጡ አስተዋፆው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ስልጠናውን የሚሰጡ ባለሙያዎች ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ እና ከትምህረት ክፍሉ በሙያው እውቀት ባላቸው መምህራን መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ስልጠናው ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የ60ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አከባበር ጋር ተያይዞ የሚሰጥ መሆን ገልጸው ኮሌጁ በተደራጁ ላብራቶሪዎች እና የመማሪያ ክፍሎች ታግዞ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ድግሪ በስፔስ ሳይንስ እያሰለጠነ መሆኑን የትምህርት ክፍሉ ሀላፊ ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ብሩክ ተረፈ ለሰልጣኞች ስለኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ የስራ እንቅስቃሴ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል፡፡
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU
ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ
Wisdom at the source of Blue Nile
Thank you for Inviting, like, share & visiting BDU page!
ለተጨማሪ መረጃዎች፡-
Telegram ፡- t.me/BDU_ISC_Official
Facebook: - https://www.facebook.com/bduethiopia
YouTube ፡- www.youtube.com/c/BduEduEt
LinkedIn ፡- www.linkedin.com/school/bahir-dar-university
Twitter: - https://twitter.com/bdueduet
Tiktok:- https://vm.tiktok.com/ZMLgRxdfL
website :- www.bdu.edu.et
website :- www.bdu.edu.e