ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን

ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን (March 08) በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተከበረ

**********************************************

(ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣የካቲት 30/2014 ዓ.ም)

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ111ኛ ጊዜ በሀገራችን ለ46ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን “Marche 8” በተለያዩ ዝግጅቶች በባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ተከበረ፡፡

ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን (March 08) በዓልን ምክንያት በማድረግ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በዋናው ግቢ  የመሰብሰቢያ አዳራሽ  የፓናል ውይይት ተካሂዷል፡፡  በውይይቱ ላይ ዶ/ር ሙሉነሽ አበበ እና ዶ/ር አልማዝ ጊዜው እለቱን አስመልክተው ለተሳታፊዎች የሕይወት ልምድና ተሞክሯቸውን አካፍለዋል፡፡

በተካሄደው የፓናል ውይይት ላይ እለቱን አስመልክቶ ለውይይት መነሻ የሚሆን ጥናታዊ ጽሁፍ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎበታል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘን  ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ተሳትፈዋል፡፡

ዘጋቢ፡- ሙሉጌታ ዘለቀ