ማስታወቂያ:- ለሁሉም መደበኛና የማታ ተማሪዎች በሙሉ

 

ጥቅምት 14 ቀን 2015 ዓ.ም

ማስታወቂያ

ለሁሉም መደበኛና የማታ ተማሪዎች በሙሉ

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የ2015 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የምዝገባ ጊዜ እንደሚከተለው መሆኑን ያሳውቃል፡፡

1ኛ በ2014 ዓ/ም አዲስ ገቢ የነበራችሁና በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ምክንያት የጀመራችሁትን ሴሚስተር ያቋረጣችሁ ሪፖርት የምታደርጉት፤

  • ለማታ ተማሪዎች ጥቅምት 18 ቀን 2015 ዓ/ም፤
  • ለመደበኛ ተማሪዎች ጥቅምት 21 እና 22 ቀን 2015 ዓ/ም ይሆናል፡፡

2ኛ ሌሎች ተማሪዎች (የ2015 አዲስ ገቢ ተማሪዎችን ጨምሮ) የመጀመሪያ ሴሚስተር ምዝገብ የሚደረገው፤

  • ለመደበኛ ተማሪዎች ጥቅምት 21 እና 22 ቀን 2015 ዓ/ም፤
  • ለማታ ተማሪዎች ጥቅምት 24 እና 25 ቀን 2015 ዓ/ም ይሆናል፡፡

 

ማሳሰቢያ፤- የ2015 ዓ/ም አዲስ ገቢ ተማሪዎች ውጤት በቅርቡ በዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር ድረ-ገጽ https://bdu.edu.et/registrar/ እና የፌስቡክ ገጽ ስለምናሳውቅ እንድትከታተሉ እያሳሰብን የተመረጡ ለምዝገባ ሲመጡ የሚከተሉትን ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡

  • ዋናውን የትምህርት ማስረጃ፤
  • የስፖንሰርሺፕ ደብዳቤ (Sponsorship Letter) በመስሪያ ቤት ስፖንሰርነት ለሚማሩ ከሚሰሩበት መስሪያ ቤት
  • የቅበላ ደብዳቤ (Admission Letter) ከድህረ-ምረቃ ት/ቤት
  • ኦፊሺያል ትራንስክሪፕት የደረሰላቸው ብቻ፤
  • ሁለት  ጉርድ ፎቶ ግራፍ፤

            ሬጅስትራርና አልሙናይ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት          

                       ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ               

Monday, October 24, 2022 (All day)