Outreach News

ኢትዮጵያ በእንስሳት ሃብት ከአፍሪካ ሀገሮች የተሻለ ደረጃ ላይ ብትገኝም በእንስሳት መኖ እጥረት ምክንያት ማግኘት የሚገባትን ጥቅም እያገኘች እንዳልሆነ የተለያዩ የመረጃ ምንጮች ያስረዳሉ፡፡ ከዚህ ችግር አኳያ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት የተለያዩ የንጥረ ነገር ውህዶችን በመጠቀም የፅንሰ-ሃሳብና የተግባር ስልጠና ለተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች በግብርናና አካባቢ ሣይንስ ኮሌጅ ግቢ ቤተ-ሙከራ ለ7 ተከታታይ ቀናት ሰጥቷል፡፡

የማዕከሉ ዳይሬክተር ዶ/ር የሻምበል መኩሪያው ቴክኖሎጅን በመጠቀም ማንኛውም ማህበረሰብ በቀላሉ አረንጓዴ የእንስሳት መኖ በአጭር ጊዜ፣ በአነስተኛ ጉልበትና ውሃ በርካታ የእንስሳት መኖ በማዘጋጀት መጠቀም የሚቻልበትን ዘዴ ለማሳወቅ ስልጠናው ፈር ቀዳጅ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ለቴክኖሎጂው ዋና ግብዓት የሆነውን ውህድ በዩኒቨርሲቲው የኬሚስትሪ ት/ክፍል ሙሁራን ተሰርቶ የቀረበ መሆኑንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ ከGIZ የእንስሳት ሃብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ የመጡት አሰልጣኝ አቶ ኃይለየሱስ አባተ የቴክኖሎጂውን ግኝትና አዋጭነት ሲገለፁ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው፣ በተለይ ዝናብ አጠርና ድርቅ በሚያጠቃቸው ቦታዎች አካባቢ በስፋት መሰራት እንደሚቻል፣ በ7 ቀናት ውስጥ ከ25-30 ሴንቲ ሜትር ርዝመት ያለው አረንጓዴ መኖ ማድረስ እንደሚቻል እንዲሁም ከ 1 ኪሎ ግራም ገብስ ከ6-10 ኪሎ ግራም የሚመዝን የእንስሳት መኖ በቀላሉ ማግኘት እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡ አሰልጣኙ አያይዘውም መኖው በተለይ ለእንቁላል ጣይ ዶሮዎች የንጥረ ነገሩ ውህድ ከፍተኛ ፕሮቲን ስላለው በርካታ እንቁላል የመጣል አቅማቸውን እንደሚያጐለብትና ስልጠናው ከሙከራ እስከ ትግበራ መሰጠቱን አስገንዝበዋል፡፡ ሰልጣኞች በባሕር ደር ከተማ የተደራጁ ሥራ አጥ ወጣቶች፣ የኮሌጁ የእንስሳት እርባታ ሠራተኞች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲውን መምህራንና የድህረ ምረቃ ተማሪዎች ሲሆኑ ከስልጠናው ከፍተኛ ግንዛቤ እንደጨበጡና በቆይታቸው መኖው ለእንስሳት መቅረብ መቻሉን ብሎም የኮሌጁ ላሞችና በጐች ሲመገቡት ማስተዋላቸውን ተናግረዋል፡፡

የኢኮ-ቱሪዝም እና ብዝሃ-ህይወት ጥበቃ ማህበር ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በቤዛዊት ቤተ መንግስት የወፍ ቆሎ (ሣንታና ካማራ) የተሰኘውን መጤ አረም ማስወገድና መልሶ ማልማት ፕሮጀክት ለማስጀመር የግማሽ ቀን አውደ-ጥናት በቤንማስ ሆቴል የመሰብሰቢያ አዳራሽ አካሄደ፡፡
ማህበሩ የኢትዮጵያ በጐ አድራጐት ማህበር ሆኖ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ በርካታ አኩሪ ተግባራትን እያከናወነ እንደሆነና የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ለማህበሩ በሰጠው 25 ሄክታር የሚሊኒየም ፓርክ ላይ ተስፋፍቶ የሚገኘውን የወፍ ቆሎ (ሣንታና ካማራ) የተሰኘውን መጤ አረም  ለማስወገድና መልሶ ለማልማት አውደ-ጥናቱ ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ከእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸው ጋር ያስተላለፉት የማህበሩ የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አያሌው ወንዴ  ናቸው፡፡
የፕሮግራሙን የመግቢያ ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙሉነሽ አበበ ጥሪውን አክብረው ለመጡት ታዳሚዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውንና ፕሮግራሙን ላዘጋጀው አካል ምስጋና አቅርበው ዩኒቨርሲቲው ከአሁን በፊት የተለያዩ መጤ አረሞችን በማጥፋት ዘመቻ በስፋት ሲሳተፍ እንደቆየ ገልፀው የወፍ ቆሎን (ሣንታና ካማራ) የተሰኘውን መጤ አረም ለማጥፋትና በሌላ አገር በቀል ዛፎች በማልማት ፓርኩ የምርምር ማዕከልና የሚጐበኝ ማራኪ ቦታ ይሆን ዘንድ እንዲሆን ዩኒቨርሲቲው ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ አስገንዝበዋል፡፡ ም/ፕሬዚዳንቷ አያይዘውም በፅንሰ ሀሳብ የቀረበው ወደ ተግባር እንዲቀየርና ፓርኩን የማልማት ሥራው እንዲጠናከር ሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ማድረግ እንዳለበት በአፅንኦት አሳስበዋል፡፡
የፕሮግራሙ ተሳታፊዎች ከተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የተውጣጡ ሙህራንና የማህበሩ አባላት ሲሆኑ 80% የሚሆኑ አባላት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች እንደሆኑ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲው ለማህበሩ መመስረትና አጠቃላይ እንቅስቃሴ ከገንዘብ ድጋፍ ጀምሮ ጉልህ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን የማህበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ትዝታ የኔአለም ተናግረዋል፡፡
በአውደ ጥናቱ ላይ የተለያዩ ጥናታዊ ፅሁፎች ቀርበው ለወደፊት ፖርኩ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ መስፋፋትና መጠናከር እንዳለበት ከቤቱ ተጠቁሞ የቀረቡት ፅሁፎች የመነሻ ሀሳብ እንደሆኑና ለሁሉም ባለድርሻ አካላት የቤት ሥራ አድርጐ እንዲወስደው ብሎም በእኔ ባይነት ስሜት ማህበሩ እንዲስፋፋ ከታዳሚዎች ሀሳብ ተሰንዝራል፡፡ 

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በግልገል አባይ ወንዝ መግቢያ ያሉ ውሃ አዘል መሬቶች ማገገምና ዘላቂ ልማት ኘሮጀክት (Rehabilitation and Sustainable Utilization of little Abay River Mouth Wetlands Project) በወንዙ ተፋሰስ ዙሪያ ያከናወናቸውን ስራዎች አስመልክቶ የአንድ ቀን ጉብኝት አካሄዷል፡፡
ኘሮጀክቱ ከተጀመረ  ሁለት ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን የአካባቢውን ውሃ አዘል መሬት መሪ እቅድ ማውጣት፣ ለአካባቢው ማህበረሰብ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ፤ በተለይ ለተማዎች እና ለተመራማሪዎች እንዲሁም ለአርሶ አደሮች፣ የደንገልን ተከላና እንክብዛቤ ማስፈን፣ የብዝሀ ህይወት ሀብት የሆነውን ጣና ሀይቅን መጠበቅ ዋና ዋና ዓላማዎች እንደሆኑ የኘሮጀክቱን በዋናነት የያዙት ሶስት የዩኒቨርሲቲው ሙህራን/ ዶ/ር ምንውየለት መንግስት፣ ዶ/ር ዋሴ አንተነህ እና ዶ/ር አማረ ሰውነት/ ገልፀዋል፡፡ ከእነዚህ አላማዎች መካከል ከ85-90 % የሚደርሱት የተከናወኑ እንደሆኑና ከዛም በዘለለ የአካባቢውን ስራ አጥ ወጣት በማደራጀት በአሳ ማስገር ሥራ ተሰማርተው እራሳቸውን እንዲችሉ ተደርጓል፡፡
በተጨማሪም ፕሮጀክቱ በአባይ ተፋሰስ አካባቢ ከ4500 ሕዝብ በላይ የሚኖርባቸው ሁለቱ ቀበሌዎችን ማለትም ከሰሜን አቸፈር ወረዳ እስቱሚት ቀበሌ እና ከባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ ልጆሚ ቀበሌ በተሻለ ዘዴ ኑሮአቸውን እንዲመሩ ለማስቻል ጉልህ አስተዋፅኦ ማበርከቱን የፕሮጀክቱ ባለቤቶች ገልፀዋል፡፡
በጉብኝቱ ወቅት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ኘሬዚዳንት ዶ/ር ሙሉነሽ አበበ የተገኙ ሲሆን ከጉብኘቱ በርካታ ያልጠበቋቸው ነገሮች ተሰርተው እንዳገኙ እንዲሁም ለወደፊቱ በደለል በመሞላት ምክንያት ተጎጅ የሆነ ያለውን የጣና ሀይቅ ለመታደግ ሁሉም እርብርብ ማድረግ እንዳለበት ገልፀው በኘሮጀክቱ አማካኝነት የተገኙትን ሁለት የሞተር ጀልባዎች ለስቱሚቱ እና ለልጆሚ ቀበሌ አስተዳደሮች አስረክበዋል፡፡ “የ CEPF(Eastern Afromontane Regional implementation Team” ) አማካሪ  የሆኑትን አቶ አብዱራሀማን ኩብሳን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው የበላይ አመራሮች ፣ ሙህራንና የአካባቢው ማህበረሰብ በጉብኝቱ ተሳትፈዋል፡፡ 

Arresting Gullies (ምርኮኛው ቦረቦር), a documentary film by the Faculty of Civil and Water Resources Engineering, BiT.

Click this link to watch...https://www.youtube.com/watch?v=Z4LhmAdjh0U&feature=youtu.be

The office of Vice president for Research and Community Services has disclosed video reports showing the major activities of research and community services carried out in 2006 & 2007 E.C. academic year.

Click the following links to watch the details...
https://www.youtube.com/watch?v=ENpL9A7FYhk
https://www.youtube.com/watch?v=Z9lPlUhnpHs&feature=youtu.be
https://www.youtube.com/watch?v=YPCF-6TD41o&feature=youtu.be

BDU: The Office of the Vice President for Research and Community Services has launched Integrated Watershed Management Community Service Center at Debremewi Village of Yilmana Densa District.

Community Services Director of the University Taye Demise said that the opening of the center will help villagers to receive capacity building training in areas of land use and management, and livelihood enhancement schemes.

According to the statement of the Office, the villagers of Debremewi will participate in experience sharing programs which are hoped will aid them to improve their productivity in agriculture.During the inaugural session at Debremawi, representatives from Bahir Dar University and villagers were present.

BDU:The Office of the Vice President for Research and Community Services has recently organized a training whose objective was to improve skill and knowledge of Women Writers.

During the function, the University’s   President Dr.Baylie Damtie, The Vice President for Information and Strategic Communication Molla Ababu and The Vice President for Research and Community Services Dr.Tesfaye Shiferaw addressed trainees.

The training was organized by the Ethiopian Women Writers’ Association Amhara Chapter in collaboration with the Vice President Office for Research and Community Services, Bahir Dar University.

Participants were members of Ethiopian Women Writers Association Amhara Chapter

TechnoServe Ethiopia has facilitated a three day practical oriented training (March 17-19, 2014) here in Bahir Dar to 62 bakers from Bahir Dar, Gondar and Mekelle. The training has focused on the products of bread, biscuit and cookies. Knowledge about ingredient types, composition, functionality, quality control and new product development has been obtained in addition to key steps in bread and biscuit processing associated with detailed discussion about process and ingredient related problems, troubleshooting and process control parameters. The trainers were highly experienced scientists and volunteers from Partners for Food Solutions (PFS) and General Mills of USA. Bahir Dar University has played its part in the training by two instructors from Food Technology and Process Engineering Program in order to assist the experienced trainers in making sure that no knowledge and skill flow from the trainers and experience sharing and questions from trainee sides were hampered due to language barriers. The food process laboratory of Bahir Dar University was used for hands on sessions. A similar training was held a week before (March 10-12) at Harmony Hotel of Addis for bakers from Addis Ababa and nearby cities and towns to benefit 68 trainees. The trainees have expressed their appreciation to all who participated in organizing such an important and problem solving training stating that they acquired a lot of knowledge that surely change the way they do business in order to profit more from baking. It is remembered that TechnoServe Ethiopia has made an agreement with Bahir Dar University to conduct five trainings each to be conducted in Addis Ababa and Bahir Dar (Hawassa). The first two trainings, “Mycotoxin Prevention and Control” and “Food Safety Management system” have been carried out in Bahir Dar and Addis by Bahir Dar University experts. The rest three trainings namely, Milling Science and Technology Bakery Science and Technology and Flour Fortification (to be conducted in June 2014) were planned to be conducted by highly experienced professionals from USA. The Bahir Dar university staffs have, in addition to filling the gap of language barrier between the trainee and trainer, benefitted from the knowledge transfer themselves and became more practical and able to sustain the knowledge and skill through teaching their students and training the community engaged in milling and baking businesses.

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጥናት ተቋም ለተቋሙ ተማሪዎች፣ መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች ሰኔ 15 እና 16 2009 ዓ.ም የመጀመሪያ የህክምና እርዳታ አሰጣጥ ስልጠና በግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ሰጠ፡፡

የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጥናት ተቋም ዋና ዓላማው አድርጐ እየሰራ ያለው መማር ማስተማር፣ ምርምር እና የማህበረሰብ አገልግሎት እንደሆነ እና ይህ የመጀመሪያ የህክምና እርዳታ ስልጠናም የማህበረሰብ አገልግሎት አንዱ አካል መሆኑን እና ስልጠናው አዳጋ ሲደርስ  በመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች የሚከሰት ጉዳትን መቀነስ እንዲቻል ታስቦ የተሰጠ እንደሆነ የተቋም መምህርና የስልጠናው አስተባባሪ አቶ ታረቀኝ አያሌው ገልፀዋል፡፡
​አስተባባሪው አክለውም በዩኒቨርሲቲውም ሆነ ከውጭ ማህበረሰብ ዘንድ የመጀመሪያ የህክምና እርዳታ እንዴት እንደሚሰጥ ግንዛቤ ባለመኖሩ የተለያዩ  ችግሮች እንደሚፈጠሩ እና ክብር የሆነው የሰው ልጅ ህይወት ለህልፈተ ሞት እንደሚዳረግ ገልፀው ስልጠናው ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል የመጡ ተማሪዎች ጨምሮ ያካተተ በመሆኑ ከራሳቸው አልፎ ለቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ለመፍጠር እንደሚያግዝና በቀላሉ ተደራሽ እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡ ሰልጣኞችም የተሰጣቸውን ስልጠና ወደ ተግባር ከመቀየር ባሻገር ለማህበረሰቡ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እንዲሰሩ አስተባባሪው ጨምረው አሳስበዋል፡፡

በአደጋ ጊዜ የሚከሰት ሞትን በመጀመሪያ እርዳታ ህክምና ከ 40 እስከ 60% መቀነስ እንደሚቻል ነገር ግን ይህ ግንዛቤ በሀገራችን አደጋ በሚከሰትበት ቦታ በፍጥነት የሚገኙትን የመከላከያ ሰራዊት እና የፖሊስ አካላት ጨምሮ ዝቅተኛ እንደሆነ በአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጥናት ተቋም መምህር እና የስልጠናው ተሳታፊ አቶ አለበል አይናለም ገልፀዋል፡፡ አቶ አለበል አክለውም የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ ለመስጠት ትምህርቱን ብቻ መማር በቂ እንዳልሆነ እና ከውስጥ የሚመነጭ ፍላጐት እንዲሁም በፍቃደኝነት ላይ የተመሰረተ መሆን እንዳለበት ጠቁመው የትምህርት ክፍሉ ወደፊት ከዩኒቨርሲቲው እና ከአካባቢው ማህበረሰብ እንዲሁም ከቀይ መስቀል ጋር በመሆን ግንዛቤ ለመፍጠር መሰራት እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡

ኢትዮጵያ በእንስሳት ሃብት ከአፍሪካ ሀገሮች የተሻለ ደረጃ ላይ ብትገኝም በእንስሳት መኖ እጥረት ምክንያት ማግኘት የሚገባትን ጥቅም እያገኘች እንዳልሆነ የተለያዩ የመረጃ ምንጮች ያስረዳሉ፡፡ ከዚህ ችግር አኳያ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት የተለያዩ የንጥረ ነገር ውህዶችን በመጠቀም የፅንሰ-ሃሳብና የተግባር ስልጠና ለተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች በግብርናና አካባቢ ሣይንስ ኮሌጅ ግቢ ቤተ-ሙከራ ለ7 ተከታታይ ቀናት ሰጥቷል፡፡

የማዕከሉ ዳይሬክተር ዶ/ር የሻምበል መኩሪያው ቴክኖሎጅን በመጠቀም ማንኛውም ማህበረሰብ በቀላሉ አረንጓዴ የእንስሳት መኖ በአጭር ጊዜ፣ በአነስተኛ ጉልበትና ውሃ በርካታ የእንስሳት መኖ በማዘጋጀት መጠቀም የሚቻልበትን ዘዴ ለማሳወቅ ስልጠናው ፈር ቀዳጅ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ለቴክኖሎጂው ዋና ግብዓት የሆነውን ውህድ በዩኒቨርሲቲው የኬሚስትሪ ት/ክፍል ሙሁራን ተሰርቶ የቀረበ መሆኑንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ ከGIZ የእንስሳት ሃብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ የመጡት አሰልጣኝ አቶ ኃይለየሱስ አባተ የቴክኖሎጂውን ግኝትና አዋጭነት ሲገለፁ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው፣ በተለይ ዝናብ አጠርና ድርቅ በሚያጠቃቸው ቦታዎች አካባቢ በስፋት መሰራት እንደሚቻል፣ በ7 ቀናት ውስጥ ከ25-30 ሴንቲ ሜትር ርዝመት ያለው አረንጓዴ መኖ ማድረስ እንደሚቻል እንዲሁም ከ 1 ኪሎ ግራም ገብስ ከ6-10 ኪሎ ግራም የሚመዝን የእንስሳት መኖ በቀላሉ ማግኘት እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡ አሰልጣኙ አያይዘውም መኖው በተለይ ለእንቁላል ጣይ ዶሮዎች የንጥረ ነገሩ ውህድ ከፍተኛ ፕሮቲን ስላለው በርካታ እንቁላል የመጣል አቅማቸውን እንደሚያጐለብትና ስልጠናው ከሙከራ እስከ ትግበራ መሰጠቱን አስገንዝበዋል፡፡ ሰልጣኞች በባሕር ደር ከተማ የተደራጁ ሥራ አጥ ወጣቶች፣ የኮሌጁ የእንስሳት እርባታ ሠራተኞች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲውን መምህራንና የድህረ ምረቃ ተማሪዎች ሲሆኑ ከስልጠናው ከፍተኛ ግንዛቤ እንደጨበጡና በቆይታቸው መኖው ለእንስሳት መቅረብ መቻሉን ብሎም የኮሌጁ ላሞችና በጐች ሲመገቡት ማስተዋላቸውን ተናግረዋል፡፡

Pages