Event Grid-2 Column
Lorem ipsum dolor sit amet, consectetur adipiscing elit, sed do eiusmod tempor incididunt ut labore et dolore magna aliqua.
13 October, 2025
From Lake Tana to the World: BDU’s Strive to Build a World-Class Maritime Center of Excellence and Make Bahir Dar a True Maritime City
From Lake Tana to the World: BDU’s Strive to Build a World-Class Maritime Center of Excellence and Make Bahir Dar a True Maritime City
08 October, 2025
የእድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ
የእድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ
ከጥቅምት 12- 15/2018 ዓ.ም ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከእስራኤል ሐገር ከሚመጡ ከፍተኛ የቀዶ ህክምና ባለሞያዎች ጋር በመተባበር በዘመናዊ መሳሪያ የታገዘ ከፍተኛ የቀዶ ህክምና (Laparoscopic Surgery) አገልግሎት ይሰጣል::
አገልግሎት የሚሰጥባቸው ዘርፎች
------------------------------------------
1. የሐሞት ጠጠር ቀዶ ህክምና (Laparascopic cholecystectomy)
2. የጉረሮ ካንሰር እና ሌሎች የጉረሮ ህመሞች ቀዶ ህክምና (Esophageal disease and other related pathologies surgery)
3. የጨጓራ ካንሰር እና ሌሎች ተያያዥ የጤና ችግሮች ቀዶ ህክምና (Gastric cancer and other gastric pathologies surgery)
08 October, 2025
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና አፍሪካን ሬነሰንስ ቴሌቪዥን (Arts TV) ስትራቴጂያዊ የሚዲያ አጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና አፍሪካን ሬነሰንስ ቴሌቪዥን (Arts TV) ስትራቴጂያዊ የሚዲያ አጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ
ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ፣ መስከረም 28/ 2018 ዓ.ም. -- ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከአፍሪካን ሬነሰንስ ቴሌቪዥን (Arts TV) ጋር በትምህርት፣ ምርምር፣ ሥራ ፈጠራና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ዙሪያ በትኩረት ለመሥራት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ የሚዲያ አጋርነት ስምምነት በይፋ ተፈራረመ። ይህ ስምምነት ሁለቱ ተቋማት የጋራ ራዕያቸውንና ዕቅዶቻቸውን በብቃት ለኅብረተሰቡ ለማድረስ ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
የአጋርነቱ ዋነኛ ዓላማ የዩኒቨርሲቲውን ትምህርታዊና ምርምራዊ ሥራዎች፣ የሥራ ፈጠራ ተነሳሽነቶችን እንዲሁም ዓለም አቀፍ ግንኙነቶችን ለሕዝብ ተደራሽ ማድረግ ነው።
01 October, 2025
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ "ሠላም አካዳሚ" የማህበረሰብ ትምህርት ቤት በይፋ አስጀመረ
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ "ሠላም አካዳሚ" የማህበረሰብ ትምህርት ቤት በይፋ አስጀመረ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ - (መስከረም 20 ቀን 2018ዓ/ም)የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎት አካል የሆነው "ሠላም አካዳሚ" የተሰኘው የማህበረሰብ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ተቀብሎ ሥራ መጀመሩን አስታወቀ። አካዳሚው የዩኒቨርሲቲውን ሠራተኞች ለመደገፍና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ያለመ ነው።
ከዚህ ቀደም በ2017 ዓ.ም. የቅድመ መደበኛ (KG 1 እስከ KG 3) ትምህርትን ሲሰጥ የቆየው ሠላም አካዳሚ፣ በዚህ ዓመት ደግሞ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን በመቀበል ሙሉ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መስጠት ጀምሯል። ይህ መስፋፋት የዩኒቨርሲቲው ለሠራተኞቹ ከሚሰጣቸው የማህበረሰብ አገልግሎቶች መካከል ዋነኛው ሲሆን፣ በተለይም የሠራተኞችን ከኑሮ ውድነት አንጻር ያለውን ጫና በማቅለል ረገድ ትልቅ ድጋፍ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
30 September, 2025
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከክልሉ መንግሥት የዋንጫ ሽልማት ተበረከተለት
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከክልሉ መንግሥት የዋንጫ ሽልማት ተበረከተለት
መስከረም 19/2018 ዓ/ም (ባሕር ዳር): ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ/ም የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ብሔራዊ ፈተና ያስፈተናቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (100%) በማሳለፉ ከአማራ ክልል መንግሥት የላቀ የዋንጫ ሽልማት ተበረከተለት።
ይህ ክብር የተጎናጸፈው በተለይ የዩኒቨርሲቲው ስቲም (STEM) ማዕከል ባስመዘገበው አስደናቂ ውጤት ነው።
የሽልማት ሥነ-ሥርዓቱ ዛሬ መስከረም 19/2018 ዓ/ም በባሕር ዳር ከተማ የተካሄደ ሲሆን፣ የዋንጫ ሽልማቱን ለዩኒቨርሲቲው ያስረከቡት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር አብዱ ሁሴን ናቸው።
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስቲም ማዕከል ለብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው 41 ተማሪዎች ውስጥ፣ ሁሉም ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባቸውን ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገብ 100% የማለፍ ውጤት አስመዝግበዋል።