From Lake Tana to the World: BDU’s Strive to Build a World-Class Maritime Center of Excellence and Make Bahir Dar a True Maritime City

13 Oct, 2025

 

From Lake Tana to the World: BDU’s Strive to Build a World-Class Maritime Center of Excellence and Make Bahir Dar a True Maritime City
 

የእድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ

08 Oct, 2025

የእድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ


ከጥቅምት 12- 15/2018 ዓ.ም ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከእስራኤል ሐገር ከሚመጡ ከፍተኛ የቀዶ ህክምና ባለሞያዎች ጋር በመተባበር በዘመናዊ መሳሪያ የታገዘ ከፍተኛ የቀዶ ህክምና (Laparoscopic Surgery) አገልግሎት ይሰጣል::

አገልግሎት የሚሰጥባቸው ዘርፎች

------------------------------------------

1. የሐሞት ጠጠር ቀዶ ህክምና (Laparascopic cholecystectomy)

2. የጉረሮ ካንሰር እና ሌሎች የጉረሮ ህመሞች ቀዶ ህክምና (Esophageal disease and other related pathologies surgery)

3. የጨጓራ ካንሰር እና ሌሎች ተያያዥ የጤና ችግሮች ቀዶ ህክምና (Gastric cancer and other gastric pathologies surgery)

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና አፍሪካን ሬነሰንስ ቴሌቪዥን (Arts TV) ስትራቴጂያዊ የሚዲያ አጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ

08 Oct, 2025

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና አፍሪካን ሬነሰንስ ቴሌቪዥን (Arts TV) ስትራቴጂያዊ የሚዲያ አጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ

ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ፣ መስከረም 28/ 2018 ዓ.ም. -- ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከአፍሪካን ሬነሰንስ ቴሌቪዥን (Arts TV) ጋር በትምህርት፣ ምርምር፣ ሥራ ፈጠራና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ዙሪያ በትኩረት ለመሥራት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ የሚዲያ አጋርነት ስምምነት በይፋ ተፈራረመ። ይህ ስምምነት ሁለቱ ተቋማት የጋራ ራዕያቸውንና ዕቅዶቻቸውን በብቃት ለኅብረተሰቡ ለማድረስ ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።

የአጋርነቱ ዋነኛ ዓላማ የዩኒቨርሲቲውን ትምህርታዊና ምርምራዊ ሥራዎች፣ የሥራ ፈጠራ ተነሳሽነቶችን እንዲሁም ዓለም አቀፍ ግንኙነቶችን ለሕዝብ ተደራሽ ማድረግ ነው።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ "ሠላም አካዳሚ" የማህበረሰብ ትምህርት ቤት በይፋ አስጀመረ

01 Oct, 2025

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ "ሠላም አካዳሚ" የማህበረሰብ ትምህርት ቤት በይፋ አስጀመረ

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ - (መስከረም 20 ቀን 2018ዓ/ም)የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎት አካል የሆነው "ሠላም አካዳሚ" የተሰኘው የማህበረሰብ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ተቀብሎ ሥራ መጀመሩን አስታወቀ። አካዳሚው የዩኒቨርሲቲውን ሠራተኞች ለመደገፍና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ያለመ ነው።

ከዚህ ቀደም በ2017 ዓ.ም. የቅድመ መደበኛ (KG 1 እስከ KG 3) ትምህርትን ሲሰጥ የቆየው ሠላም አካዳሚ፣ በዚህ ዓመት ደግሞ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን በመቀበል ሙሉ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መስጠት ጀምሯል። ይህ መስፋፋት የዩኒቨርሲቲው ለሠራተኞቹ ከሚሰጣቸው የማህበረሰብ አገልግሎቶች መካከል ዋነኛው ሲሆን፣ በተለይም የሠራተኞችን ከኑሮ ውድነት አንጻር ያለውን ጫና በማቅለል ረገድ ትልቅ ድጋፍ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከክልሉ መንግሥት የዋንጫ ሽልማት ተበረከተለት

30 Sep, 2025

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከክልሉ መንግሥት የዋንጫ ሽልማት ተበረከተለት

መስከረም 19/2018 ዓ/ም (ባሕር ዳር): ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ/ም የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ብሔራዊ ፈተና ያስፈተናቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (100%) በማሳለፉ ከአማራ ክልል መንግሥት የላቀ የዋንጫ ሽልማት ተበረከተለት።

ይህ ክብር የተጎናጸፈው በተለይ የዩኒቨርሲቲው ስቲም (STEM) ማዕከል ባስመዘገበው አስደናቂ ውጤት ነው።

የሽልማት ሥነ-ሥርዓቱ ዛሬ መስከረም 19/2018 ዓ/ም በባሕር ዳር ከተማ የተካሄደ ሲሆን፣ የዋንጫ ሽልማቱን ለዩኒቨርሲቲው ያስረከቡት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር አብዱ ሁሴን ናቸው።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስቲም ማዕከል ለብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው 41 ተማሪዎች ውስጥ፣ ሁሉም ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባቸውን ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገብ 100% የማለፍ ውጤት አስመዝግበዋል።

We are pleased to announce that registration for the 2018 NGAT has now started!

Submitted by TANA on

Register here: https://ngat.ethernet.edu.et

Please take note of the following important points:

1. Ethiopian applicants must have a National ID (Fayda) to complete the registration process.

2. There will be no specialty categories this year. The exam will be the same for all candidates, regardless of educational background.

በአፍላቶክሲን ብክለት ላይ የሚደረገውን ትግል የሚያግዝ ተስፋ ሰጪ አዲስ መሣሪያ በባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተመራማሪዎች ይፋ ተደረገ

25 Sep, 2025

በአፍላቶክሲን ብክለት ላይ የሚደረገውን ትግል የሚያግዝ ተስፋ ሰጪ አዲስ መሣሪያ በባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተመራማሪዎች ይፋ ተደረገ 

(መስከረም 15/2018ዓ.ም ISC/BiT) በአፍላቶክሲን ብክለት ላይ የሚደረገውን ትግል የሚያግዝ ተስፋ ሰጪ አዲስ መሣሪያ በባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተመራማሪዎች ፣ ዊዝደም ኢንተርፕራይዝ ከ Stichting Wageningen Research (SWR) Ethiopia's RAISE-FS project ባገኘው የኢኖቬሸን ፈንድ ድጋፍ ታግዞ ይፋ ተደርጎ በዛሬው ዕለት ለአውደ ርዕይ ቀርቧል። ይህ አዲስ ፈጠራ፣ ቀላል፣ ወጪ ቆጣቢ የሆነው የእርጥበት መለኪያ ኪት፣ የደረቁ ምግቦችንና መኖ ምርቶችን ከብክለት ለመከላከል ታስቦ የተዘጋጀ ነው።

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አሳታሚ ድርጅት አቋቋመ

17 Sep, 2025

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አሳታሚ ድርጅት አቋቋመ
የመጀመሪያ ሥራው የአፄ ዘርአ ያዕቆብ ዜና መዋዕል ሆነ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መጻሕፍትን በማዘጋጀትና በማሳተም ለማሰራጨት የሚያስችለውን “ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ” የተሰኘ አሳታሚ ድርጅት ማቋቋሙን አስታወቀ። ፕሬሱ የመጀመሪያ ሥራው አድርጎ “የዐፄ ዘርአ ያዕቆብ ዜና መዋዕል (1426 - 1460 ዓ.ም) ግእዝ-አማርኛ ትርጉም እና ሐተታ” የተሰኘ መጽሐፍ አሳትሞ ለገበያ አብቅቷል።
ይህ መጽሐፍ ከግእዝ ወደ አማርኛ የተተረጎመ ሲሆን፣ የመካከለኛውን ዘመን ታላቁን ንጉሥ አፄ ዘርአ ያዕቆብ የዘመን ታሪክና የእለት ከዕለት እንቅስቃሴ በዝርዝር ያቀርባል። 157 ገጾችን የያዘው ይህ ታሪካዊ ሰነድ፣ በመካከለኛው ዘመን የኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ለሚደረጉ ጥናቶች ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተገልጿል።
መጽሐፉ በአሁኑ ጊዜ በባሕር ዳር ከተማ በሚገኙ የመጻሕፍት መደብሮች በ350 ብር እየተሸጠ ሲሆን፣ በቅርቡ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በደማቅ ሥነ ሥርዓት የሚመረቅ ይሆናል።

ለመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

Submitted by TANA on

መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም
ማስታወቂያ
ለመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው የመግቢያ መስፈርት መሰረት በመደበኛ መርሃ ግብር በግላቸው ከፍለው በመደበኛው መርሃግብር የመጀመሪያ ዲግሪ መማር የሚፈልጉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም መስፈርቱን የሚያሟሉና በግላችው ከፍለው መማር የሚፈልጉ አመልካቾች መስከረም 6 ቀን 2018 ዓ/ም እስከ  መስከረም 12 ቀን  2018 ዓ/ም ድረስ የሚፈልጉትን የትምህርት ፕሮግራም (Department) በመምረጥ ማመልከት የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
የመግቢያ መስፈርት
-  በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ወስደው የከፍተኛ ትምህርት  መግቢያ መቁረጫ ነጥብ ያሟሉ፤
-  በ2017 ዓ.ም የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ወስደው የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብ ያላቸው፤