News

ክፍት የኅላፊነት ቦታ ማስታወቂያ

ክፍት የኅላፊነት ቦታ ማስታወቂያ 
===================
18/06/2016 ዓ.ም 

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዩኒቨርሲቲው ባወጣው አዲስ የመካከለኛ አመራሮች መመደቢያ መመሪያ መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ የኮሌጁ የጤና ትምህርት ኮርፓሬት ም/ድሬክተር (Deputy Corporate Director, Medical and Health Science Education) ቦታ መመደብ ይፈልጋል፡፡ 

የማወዳደሪያ መሥፈርት 
==============

1ኛ. የትምህርት ደረጃ ሦስተኛ ዲግሪ/ስፔሻሊቲ ሰርተፊኬት (ወይም አቻ ) እና ረዳት ፕሮፌሰር እና ከዚያ በላይ ማዕረግ ያለው/ያላት፣  
2ኛ. በከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ በጥናትና ምርምር ወይም መሰል ተቋማት፣ በመማር ማስተማር፣ ሕክምናና ማኅበረሰብ አገልግሎት ወይም መሰል ተልዕኮ ባላቸው ተቋማት በልዩ ልዩ ኃላፊነት እርከን ያገለገለ/ችና ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረከተ/ች፣  
3ኛ. በሚያመለክቱበት ዘርፍ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የጤና ትምህርት  ተደራሽነት፣ ፍትሐዊነት፣ ጥራትንና ደኅንነት፣ ተገቢነትና ዓለም አቀፋዊነትን ለማሳካት፣ ኮሌጁን የጤና ትምህርት የልህቀት ማዕከል ለማድረግ እና ክሱትነቱን ለመጨመር፣ ተጨማሪ ሀብት ለማስገኘት፣ እንዲሁም ዓለም አቀፋዊና አገራዊ ጉድኝቶችን ለመፍጠርና ለማስፋት በሚደረገው ሂደት አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችል አጭር ስትራቴጅያዊ (ስልታዊ) ዕቅድ ማዘጋጀትና ማብራሪያ መስጠት የሚችል/የምትችል፣  
4ኛ. ከኮሌጁ የሚሰጠውን ዝርዝር ኃላፊነት በቅንነት፣ በትጋትና በታማኝነት ተቀብሎ  በከፍተኛ ብቃት የሚፈፅም፣ 
5ኛ. የኮሌጁ አመራሮች፣ የማኔጅመንት አባላት፣ የኮሌጁ መምሕራን ተወካዮች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተጋብዘው በሚገኙበት መድረክ በአጀንዳዎች ላይ በአካል ተገኝቶ/ታ ማብራሪያና ገለፃ መስጠት የሚችል/የምትችል፣ 
6ኛ. ከትምህርት ወይም ምርምር ወይም ሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ መደበኛ የሥራ እረፍት ላይ ያልሆነ/ች እና ለቀጣይ ሦስት ዓመት በኃላፊነት ለማገልገል ፈቃደኛ የሆነ/ች::

አመልካቾች፡- ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን (18/06/2016ዓ.ም) ጀምሮ ባሉት ዐሥራ አምስት (15) ተከታታይ የሥራ ቀናት የሚከተሉትን ሰነዶች ማለትም 
1. ማመልከቻ ደብዳቤ፣
2. ግለ ታሪክ('CV')፣ 
3. የትምህርትና የሥራ/አመራርነት ልምድ (በሰው ሀብት አስተዳድር ልማት ቢሮ የረጋገጠ) ማስረጃ ፎቶ ኮፒ  እንዲሁም
4. ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ስትራቴጅያዊ ዕቅድ
በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ድሬክተር ቢሮ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ 

የመመዝገቢያ ቦታ 
==========
ጥበበ ግዮን ካምፓስ
ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲ
ባሕር ዳር

ክፍት የኅላፊነት ቦታ ማስታወቂያ

ክፍት የኅላፊነት ቦታ ማስታወቂያ 
==================
18/06/2016 ዓ.ም 

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዩኒቨርሲቲው ባወጣው አዲስ የመካከለኛ አመራሮች መመደቢያ መመሪያ መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ የኮሌጁ የጥናት፣ ምርምር እና ማኅበረሰብ አገልግሎት ኮርፖሬት ድሬክተር (Corporate Director, Research, Development and Community Services) ቦታ መመደብ ይፈልጋል፡፡ 

የማወዳደሪያ መሥፈርት 
==============

1ኛ. የትምህርት ደረጃ ሦስተኛ ዲግሪ/ስፔሻሊቲ ሰርተፊኬት (ወይም አቻ ) እና ረዳት ፕሮፌሰር እና ከዚያ በላይ ማዕረግ ያለው/ያላት ፣  
2ኛ. በከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ በጥናትና ምርምር ወይም መሰል ተቋማት፣ በመማር ማስተማር፣ ማኅበረሰብ አገልግሎት ወይም መሰል ተልዕኮ ባላቸው ተቋማት በልዩ ልዩ ኃላፊነት እርከን ያገለገለ/ችና ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረከተ/ች፣  
3ኛ. በሚያመለክቱበት ዘርፍ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የጥናትና ምርምር እና ማኅበረሰብ አገልግሎት ተደራሽነት፣ ፍትሐዊነት እና ችግር ፈችነት፣ ጥራትንና ደኅንነት፣ ተገቢነትና ዓለም አቀፋዊነትን ለማሳካት፣ ኮሌጁን ድህረ ምረቃ መር የልህቀት ማዕከል ለማድረግ እና ክሱትነቱን ለመጨመር፣ ተጨማሪ ሀብት ለማስገኘት ፣ እንዲሁም ዓለም አቀፋዊና አገራዊ ጉድኝቶችን ለመፍጠርና ለማስፋት በሚደረገው ሂደት አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችል አጭር ስትራቴጅያዊ (ስልታዊ) ዕቅድ ማዘጋጀትና ማብራሪያ መስጠት የሚችል/የምትችል፣  
4ኛ. ከኮሌጁ የሚሰጠውን ዝርዝር ኃላፊነት በቅንነት፣ በትጋትና በታማኝነት ተቀብሎ  በከፍተኛ ብቃት የሚፈፅም፣ 
5ኛ. የኮሌጁ አመራሮች፣ የማኔጅመንት አባላት፣ የኮሌጁ መምሕራን ተወካዮች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተጋብዘው በሚገኙበት መድረክ በአጀንዳዎች ላይ በአካል ተገኝቶ/ታ ማብራሪያና ገለፃ መስጠት የሚችል/የምትችል፣ 
6ኛ. ከትምህርት ወይም ምርምር ወይም ሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ መደበኛ የሥራ እረፍት ላይ ያልሆነ/ች እና ለቀጣይ ሦስት ዓመት በኃላፊነት ለማገልገል ፈቃደኛ የሆነ/ች::

አመልካቾች፡- ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን (18/06/2016ዓ.ም) ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የሥራ ቀናት የሚከተሉትን ሰነዶች ማለትም 
1. ማመልከቻ ደብዳቤ፣
2. ግለ ታሪክ('CV')፣ 
3. የትምህርትና የሥራ/አመራርነት ልምድ (በሰው ሀብት አስተዳድር ልማት ቢሮ የረጋገጠ) ማስረጃ ፎቶ ኮፒ  እንዲሁም
4. ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ስትራቴጅያዊ ዕቅድ
በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ድሬክተር ቢሮ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ 

የመመዝገቢያ ቦታ 
==========
ጥበበ ግዮን ካምፓስ
ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

Public Lecture

ማስታወቂያ

30/08/2015ዓ.ም

ማስታወቂያ/Vacancy/

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዩኒቨርሲቲው ባወጣው አዲስ የመካከለኛ አመራሮች መመደቢያ መመሪያ መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ የጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ምክትል የሚድዋይፍሪ አገልግሎት ዲሬክተር (Vice Director, Midwifery Services) ቦታ መሾም ይፈልጋል፡፡

የማወዳደሪያ መስፈርት
----------------------

1ኛ. የትምህርት ደረጃ የመጀመሪያ ዲግሪ/ከዚያ በላይ የትምህርት ደረጃ ያለው/ያላት፣
2ኛ. በከፍተኛ ትምህርት/ጤና ተቋም፣ በሆስፒታል፣ በኢንዱስትሪ፣ በምርምር ተቋማት በመማር ማስተማር፣ ማህበረሰብ አገልግሎት ወይም መሰል ተልዕኮ ባላቸው ተቋማት በልዩ ልዩ ሀላፊነት እርከን ያገለገለ/ችና ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረከተ/ች ወይም ዉጤት ያመጣ/ያመጣች፣
3ኛ. በሚያመለክቱበት ዘርፍ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የነርስ አግልግሎትን እና ተደራሽነትን፣ ፍትሃዊነት፣ ጥራትን፣ ተገቢነትንና ዓለም አቀፋዊነትን ለማሳካት፣ ኮሌጁን፣ ሆስፒታሉንና ትምህርት ቤቶችን የልህቀት ማዕከል ለማድረግ፣ ተጨማሪ ሀብት ለማስገኘት፣ እንዲሁም ዓለም አቀፋዊና አገራዊ ጉድኝቶችን ለመፍጠርና ለማስፋት በሚደረገው ሂደት አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችል አጭር ስትራቴጅያዊ ዕቅድ ማዘጋጀትና ማብራሪያ መስጠት የሚችል/የምትችል፣
4ኛ. ከኮሌጁ የሚሰጠውን ዝርዝር  ሃላፊነት በጥበብ፣ በቅንነት፣ በቁርጠኝነት እና በታማኝነት ተቀብሎ የሚፈፅም፣
5ኛ. የሆስፒታሉ አመራሮች፣ የሆስፒታሉ ማኔጅመንት አባላት፣ ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተጋብዘው በሚገኙበት መድረክ በአጀንዳዎች ላይ በአካል ተገኝቶ/ታ ማብራሪያና ገለፃ መስጠት የሚችል/የምትችል፡፡

አመልካቾች፡- ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን (30/08/2015ዓ.ም) ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት የትምህርትና የሥራ ልምዳቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ያዘጋጁትን ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ስትራቴጅያዊ ዕቅድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዲሬክተር ቢሮ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡

የመመዝገቢያ ቦታ
------------------
ጥበበ ግዮን ካምፓስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዲሬክተር ቢሮ
ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

Friday Seminar

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና ሆስፒስ ኢትዮጵያ በጋራ ለመስራት ተስማሙ!

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ
እና ሆስፒስ ኢትዮጵያ በጋራ ለመስራት ተስማሙ!
------------------------
የትብብሩ ዋና ዓላማ ሁለንተናዊ የሆነ የሕመም ስቃይ እፎይታ እንክብካቤ (Comprehensive Palliative Care) አገልግሎት በጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ እንዲጀመር በማድረግ አገልግሎቱን ለማሕበረሰቡ ተደራሽ ማድረግ ነው፡፡
አብረውን በመስራት ከፍተኛ ህመምንና የህመም ስቃይን ለመቀነስ ሀገር አቀፍ እንቅስቃሴ የሚያደርጉትን ሆስፒስ ኢትዮጵያን በሕሙማን ስም ከልብ እናመሰግናለን!
የጋራ ጥረት ለማሕበረሰብ ጤንነት!

ኮሌጅ በሶስተኛ ዙር ያሰለጠናችዉን ሰባት የማህፀንና ጽንስ ሕክምና ስፔሻሊስት እጩ ሐኪሞች አስፈተነ

የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሰባት የማህፀንና ጽንስ ሕክምና ስፔሻሊስት ሐኪሞችን በዉጭ ፈታኞች አስገምግም በ14/04/2012 አስጨርሷል:: ኮሌጁ ማሰልጠን ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ 20 የማህፀንና ጽንስ ሕክምና ስፔሻሊስት ሀኪሞችን በሶስት ዙር አስመርቋል:: የአራት ዓመት የትምህርት ጊዜያቸዉን በድል ያጠናቀቁ ተመራቂ ስፔሻሊስት ሐኪሞችን እንኳን ደስ ያላችሁ እያለ አስተምረው ለዚህ ደረጃ ያበቁ መምህራንንም ኮሌጁ ከልብ ያመሰግናል:: የሴቶችን ጤና በመጠበቅና የስነ ተዋልዶ ዘርፉን በማሳለጥ በተለይም በወሊድ ምክንያት የሚከሰትን የእናቶች ሞት በመቀነስ ረገድ መሪ ተዋናኝ በመሆን ለማህበረሰብ ጤናና እድገት የበኩላችሁን እንደምትወጡ እምነታችን የፀና ነው:: መልካም የስራ ዘመን!

Pages

Contact CMHS

College Of Medicine and Health Sciences

Bahir Dar University

 Bahir Dar, Ethiopia

Phone:- +251-0582-9 99275

P.o.box:- 79

e-mail:- collegehealthscience@gmail.com

Institutes

Website Design and Developed by LTTU,ICT Copyright © 2017- Bahir Dar University