Latest News

6ኛው ዓለም አቀፍ ዓመታዊ የመሬት ጉባኤ ተካሄደ
******************************
ግንቦት 25/2015 ዓ/ም፤ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ] የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመሬት አስተዳደር ተቋም ከኢትዮጵያ መሬት አሥተዳደር የባለሙያዎች ማኅበር ጋር በመተባበር "የኢ-ላንድ አስተዳደርን ለመልካም አስተዳደርና ለዘላቂ ልማት ማስተዋወቅ“ በሚል መሪ ቃል 6ኛው ዓለም አቀፍ ዓመታዊ የመሬት አውደጥናት የአማራ ክልል የመሬት ቢሮ ሃላፊ ፣ የዘርፉ ባለሙያዎች እና ምሁራን በተገኙበት በባሕር ዳር ከተማ ዩኒሰን ሆቴል ተካሂዷል፡፡
በጉባኤው መክፍቻ ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመሬት አስተዳደር ተቋም ዲን ዶ/ር በላቸው ይርሳው እንዳሉት በመሬት አስተዳደር ዙሪያ ፖሊሲዎችን ለማውጣት ከፍተኛ አቅም የሚፈጥር ፤ በቴክኖሎጂ ታግዞ በአግባቡ የተጠናከረ መረጃ ለማስቀመጥና ብሎም የሀገሪቱን የመሬት አያያዝ፣ አጠቃቀም እና አሥተዳደር ለማዘመን አስተዋፆው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የመሬት አያያዝና አጠቃቀምን ለማዘመን ኢንስቲትዩቱ በየዓመቱ ተማሪዎችን ከማብቃት በተጨማሪ ለተለያዩ ባለሙያዎች አጫጭር ሥልጠናዎችን አዘጋጅቶ መስጠቱን እና በሀገሪቱ ከመሬት ጋር ተያይዞ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታትም ከሚመለከታቸው የመንግሥትና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በጋራ እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በአውደጥናቱ ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ የባሕረ ዳር ከተማ የጣና ፎረም የምክክር መድረክን ጨምሮ በርካታ ሀገርአቀፍ እና ዓለምአቀፍ ጉባኤዎችን የምታስተናግድ መሆኗን ጠቅሰው ለግዙፉ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መነሻው የቀድሞው የባሕር ዳር ፖሊ ቴክኒክ ኢንስቲትዩት እና የባሕር ዳር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከምስረታው ጀምሮ እሰካሁን ባለው በመማር ማስተማር በምርምሩ ዘርፍ ካበቃቸው ሙሁራን በተጨማሪ የሚሰጣቸውን የትምህርት ፕሮግራሞች በየጊዜው በማሳደግ በአሁኑ ሰዓት ከ429 በላይ ፕሮግራሞች ፣ በስድስት ፕሮግራሞች የልዕቀት ማዕከል፣ ከ232 በላይ አጋር ተቋማት ያሉት እና በጠንካራ አመራር እና ልምዱ ቀዳሚ እና ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከታጩ ቀዳሚ የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች መካከል አነዱ ሆኖ መመረጡን ዶ/ር ፍሬው ተናግረዋል፡፡
በአውደጥናቱ መክፈቻ ላይ የአማራ ክልል መሬት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሲሳይ ዳምጤ እንዳሉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመሬት አስተዳደር ተቋም በሚሰራቸው የምርምር ስራዎች እና በየዓመቱ እያስመረቀ በሚያወጣቸው ባለሙያዎች አማካኝነት የክልሉ የመሬት አስተዳደር ስረዓት በእጅጉ እየዘመነ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ በየዓመቱ መሬትን አስመልክቶ በሚያካሂደው አውደጥናት ላይ የሚቀርቡ የምርምር ውጤቶችን የክልሉ መንግስት የእቅዱ አካል በማድረግ በሁሉም ዞኖች ተግባራዊ በማድረግ ላይ መሆኑን ጠቅሰው በአሁኑ ሰዓት 18 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር የተበጣጠሰ የገጠር መሬት በ4 ነጥብ 3 ሚሊዮን አባውራዎች ይዞታ ሥር ይገኛል፡፡ ከዚህም ውስጥ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በተሠራው ዘመናዊ የመሬት አሥተዳደር ሥራ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ አባወራዎች ይዞታ ስር የሚገኝ ከ11 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር በላይ የተበጣጠሰ መሬት የማረጋገጫ ደብተር እየተሰራላቸው መሆኑን አቶ ሲሳይ ዳምጤ ተናግረዋል፡፡
በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ዲዛይን ተባባሪ ፕሮፌሰር እና የስራ ሃላፊ የሆኑት ዶ/ር ዳንኤል ላሬቦ በበኩላቸው ኢትዮጵያ የገጠር እና የከተማ መሬት በአግባቡ ከዘራፊዎች እጅ በማውጣት የህዝብ ተጠቃሚነትን እና ዘላቂ የልማት አቅጣጫዎች እንዲቀመጡ ከማድረግ አኳያ የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ የመሬት አስተዳደር ተቋም በየዓመቱ የሚያካሂዳቸው አውደጥናቶች ሚናቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተባበሩት መንግስታት ዘላቂ የልማት ግቦች ከሚባሉት ውስጥ የመሬት አስተዳደር ጉዳይ አንዱ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ኢትዮጵያም ለማሳካት ዩኒቨርሲቲዎች የዩኒቨርሲቲ ኢንደስትሪ ትስስር በመፍጠር ከተቋማቶች ጋር መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ በመሬት አጠቃቀም ዙሪያ የሚታዩ ችግሮችን መነሻ በማድረግ የኢ-ላንድ አስተዳደርን ለመልካም አስተዳደርና ለዘላቂ ልማት ማስተዋወቅን አስመልክቶ ለጉበኤ ታደሚዎች ቁልፍ ንግግር አድርገዋል።
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመሬት አስተዳደር ተቋም አዘጋጅነት "የኢ-ላንድ አስተዳደርን ለመልካም አስተዳደርና ለዘላቂ ልማት ማስተዋወቅ" በሚል መሪ ሀሳብ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በተካሄደው ጉባኤ ላይ የመሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም፣ የመሬት መረጃ አያያዝ በቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆን እና ቀጣይነት እንዲኖረው ማድረግ እና የመሬት አስተዳደር ፓሊሲና ሕግን በተመለከተ 13 የጥናት ወረቀቶች ቀርበው የጉባኤው ተሳታፊ ሰፊ ክርክርና ውይይት አድርገዋል፡፡
በጉባኤው ማጠቃለያ ላይ ከተለያዩ ተቋማት በመምጣት በአውደጥናቱ ላይ ጥናታዊ ወረቀት ያቀረቡ እና ለአውደጥናቱ መሳካታ የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ giz እና USAID እና የኢትዮጵያ መሬት አሥተዳደር የባለሙያዎች ማኅበር በዩኒቨርሲቲው የምርመር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዚዳንት ከዶ/ር ተስፋዬ ሽፈራው እጅ የእውቅና ሰረትፊኬት ተበርክቶላቸዋል፡፡
 
Asnaqu Dagne was the first female graduate of Poly-Technic Institute, BDU-BiT, in Industrial Chemistry in 1963 E.C. Unique to the previous 4 batches, the 1963 E.C. class were admitted from grade 12 and graduated together with those admitted from grade 10 because of curriculum reform. Asnaku belonged to those admitted from grade 12 for the first time.

Teacher Abeba Gela who was class of 1981 and has been serving her country for the past four decades as a teacher and in different administrative capacities and her husband Mr. Birara Ayenew handed over 104 collection of books to Bahir Dar University in the presence of the president of the University, Dr. Firew Tegegne.

Anniversary Memories:

The first batch of Bahir Dar Poly Technic Institute students graduated on Sene 25, 1959 E.C in the presence of Emperor Haileselassie, Ambassador Leonid Teplov (USSR Ambassador to Ethiopia) and other dignitaries like Crown Prince Assfaw Wossen, Prince Imiru Haileselassie, Prince Wossen Seged Mekonnen, Commander Iskinder Desta (Vice commander of Navy), Lij Kassa Woldemariam (President of Haileselassie I University), Akaleworq Habtewold (Minister of Education and Fine Arts), Million Neqiniq (Vice Minister of Education  and Fine Arts), Ambassador Yilma Deressa (Minister of Finance), Dr.Haile Giorgis Worqineh (Vice Minister of Labor), and Tsehafe Tizaz Tefera-Worq Kidanewolde (Minister of Palace).

Among the 232 students admitted as freshmen, only 151 managed to complete their studies of whom Tesfaye Biftu, now Professor, seen below in the picture receiving his diploma from H.I.M Haileselassie, completed top from his  Industrial Chemistry program and received gold medal.

The professor has became the most influential medicinal chemist in he USA at present. He was the program lead and key innovator in the discovery of 12 drug candidates including Marizev™, the Once Weekly DPP-4 Inhibitor anti-diabetic agent, and key player in the Januvia™ project which has a total sales over 70 billion since its introduction in 2006. He has more than 95 patents registered in his name.

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ተቋም የቆዳና የአልባሳት ምርቶችን ለኤግዚቪሽን አቀረበ

******************************************************************

በባሕር ዳር ከተማ አለ በጅምላ ግቢ በተዘጋጀው የትንሳኤ እና የኢድ ዋዜማ የንግድ ትርኢትና ባዛር ላይ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ተቋም በተማሪዎች ዲዛይን የተደረጉ የቆዳና የአልባሳት ውጤቶችን ለእይታ አቅርቧል፡፡

በኤግዚቪሽኑም ከቆዳና ከጨርቃ ጨርቅ የተሰሩ ጃኬቶች፣ ጫማዎች፣ ቦርሳዎች፣  የህፃናት  ማዘያና  መሰል  ምርቶች ለእይታ ቀርበዋል፡፡

ምርቶቹን ሲመለከቱ ያገኘናቸውና ስለምርቶቹ አጠቃላይ ሁኔታ የጠየቅናቸው ዶ/ር ፀሐይ ነጋ እንደነገሩን አልባሳቱ ለተለያየ ዓላማ  እንድንጠቀምባቸው ታስበው በመሰራታቸው ለአጠቃቀም ቀላልና ምቹ ናቸው ብለዋል፡፡ ዲዛይነሮቹ በደንብ ቢታገዙ፣ ቴክኖሎጂው ቢሻሻልና የተሻለ ስልጠና ቢሰጥ ከዚህ የተሻለ ነገር እንደሚሰራ አምናለሁ ብለዋል፡፡ ዶ/ር ፀሐይ አክለውም ምርቶች ላይ ስራ ከመስራታችን አስቀድሞ አመለካከት ላይ መሰራት አለበት ያሉ ሲሆን ምርቶች የትም ሀገር ይመረቱ መታየት ያለበት ጥራታቸው ነው፤ ስለሆነም በሀገራችን ተወዳዳሪ ምርት በማምረት ልክ ህንድን እንደመሰሉ ሀገራት የሀገራችንን ምርት መጠቀም ይኖርብናል ብለዋል፡፡

ሌላው አስተያየታቸውን የሰጡን አቶ ጌታሁን ስዩም ይባላሉ፡፡ ከባሕር ዳር  ከተማ  እንደመጡ ነግረውን  የተሰሩት ስራዎች በጣም ጥሩዎች መሆናቸውን ገልፀው፤ ሆኖም የኢንዱስትሪ ሽግግር እንዲኖር ዩኒቨርሲቲው ከባለሀብቶች ጋር በጋራ መስራት ይኖርበታል ብለዋል፡፡ አክለውም ተማሪዎችን በሚገባ ማብቃትና ትልልቅ ማሽኖችን መጠቀምም ስራውን የበለጠ ለማዘመን ያግዛል ብለዋል፡፡

ምርቶቹን ለተመልካቾች በማቅረብ የማስተዋወቅ ስራ እየሰሩ ያገኘናቸው ወ/ሮ ኑኑሸት ምትኩ ህብረተሰቡ ጥሩ አስተያየት እየሰጠ መሆኑን ነግረውናል፡፡ ይሁን እንጂ ምርቶቹ ለሽያጭ መቅረብ እንዳለባቸው ብዙ አስተያየት ሰጭዎች እንደነገሯቸው አክለው ገልፀውልናል፡፡

 

‹‹የተማሪዎችን ሁለንተናዊ ዕድገት በማረጋገጥ ጤናማ እና አምራች ዜጋን መፍጠር ቀዳሚ ተግባራችን ነው›› አቶ ኤርሚያስ ዘውዱ የሆፕ ፎር ኢትዮጵያ መስራችና ስራ አስፈፃሚ

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ከሆፕ ፎር ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ውስጥ በሚገኙ 24 ትምህርት ቤቶች (ከኬጅ እስከ መሰናዶ ትምህርት ቤት) ከሚተገብራቸው 5 ዘርፎች የተማሪዎች የጤና መረጃ አያያዝ ስልጠና ለነርሶች መስጠት ጀመረ፡፡

በስልጠና ማስጀመሪያው ላይ የተገኙት የሆፕ ፎር ኢትዮጵያ መስራችና ስራ አስፈፃሚ አቶ ኤርሚያስ ዘውዱ ባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ውስጥ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ድርጅቱ የሚያከናውናቸው ተግባራት ንፅህና አጠባበቅ ፕሮቶኮል፣ በትምህርት ቤት የጤና አገልግሎት አቅርቦት፣ በትምህርት ቤት ቀጣይነት ያለው የተመጣጠነ የምግብ ፕሮግራም፣  በትምህርት ቤት የስፖርት መገልገያዎች እና ቁሳቁሶች ግንባታና አቅርቦት፣ በትምህርት ቤት የአትሌቲክስ ስልጠና እና ልማት ፕሮግራሞች እንደሆኑ ገልፀዋል፡፡

አቶ ኤርሚያስ ፕሮግራሙ በከተማው በሞዴልነት በተመረጡ የጣና ሐይቅ 2ኛ ደረጃ መሰናዶ እና የጠይማ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደሚጀምር ተናግረዋል፡፡ በዚህም ትምህርት ቤቶችን ምቹ የትምህርት አካባቢ በማድረግ ጤናማ እና አምራች ዜጋን መፍጠር እንችላለን ብለዋል፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የስፖርት አካዳሚ ዲን ዶ/ር ዳኛቸው ንግሩ በበኩላቸው ከሆፕ ፎር ኢትዮጵያ ጋር የአምስት ዓመት መርሃ ግብር ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መገባቱን አውስተዋል፡፡ ለዚህም ፕሮግራም መሳለጥ አስተዋጾ ያደረጉትን የዩኒቨርሲቲውን ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ፕሬዝዳንት ፅ/ቤት፣ የአባይ ማዶ አዲስ አለም ሆስፒታል፣ ለባሕር ዳር ጤና መምሪያ፣ ለኦርቤት ሄልዝ እና አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ምስጋቸውን አቅርበዋል፡፡

የጤና መረጃ አያያዝ ስልጠና ለነርሶች እየሰጡ የሚገኙት የ Orbit Health Domain Expert ዶ/ር ዳኛቸው የዛሬው ስልጠና የሚያተኩረው የተማሪዎች ጤና መመዝገቢያ ፕሮግራም ውጤታማ ለማድረግ ነርሶች በቴክኖሎጅ እየታገዙ ተማሪ ቤት እና ሆስፒታል በቅንጅት የሚሰሩበት ነው ብለዋል፡፡

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile
ለተጨማሪ መረጃዎች፡-
Facebook https://www.facebook.com/bduethiopia
YouTube https://www.youtube.com/@bduethiopia
Instagram www.instagram.com/bduethiopia
TikTok https://www.tiktok.com/@bduethiopia
Telegram https://t.me/bduethiopia
Twitter https://twitter.com/bduethiopia
LinkedIn http://www.linkedin.com/school/bduethiopia
Website https://bdu.edu.et/
#bdu60th_anniversary

ኢትዮጵያ በዩኒስኮ ካስመዘገበቻቸው ዘጠኝ ቅርሶች መካከል ሶስቱ በአማራ ክልል እንደሚገኙ ተገለፀ

የሰላም ሚኒስቴር ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የሚያሰለጥናቸው የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች የባህል ትውውቅ መድረክ በስራ አመራር አካዳሚ አዳራሽ በድምቀት ተካሂዷል፡፡

በትውውቅ መድረኩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አየለ አናውጤ ለመድረኩ ተሳታፊዎች እንደገለፁት አማራ ክልል በርካታ ብሄር ብሄረሰቦችን የያዘ፤ ከ20 በላይ ዞኖችና ሪጂኦ ፖሊታን ከተሞች የተዋቀረ፤ በርካታ ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊ፣ ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ ቅርሶችን የያዘ ክልል ነው ብለዋል፡፡ክልሉ ስያሜው የአማራ ክልል ይሁን እንጂ የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦችን አቅፎ የያዘ ክልል ነው የሚሉት ዶ/ር አየለ ለበርካታ ብሄር ብሄረሰቦች እውቅና በመስጠት የመንግስታዊ መዋቅሩ አካል ያደረገ ክልል ነው ብለዋል፡፡ለዚህም ለኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን፣ ለአዊ ብሄረሰብ ዞን፣ ለዋገኸምራ ብሄረሰብ ዞን እና ለአርጎባ ልዩ ወረዳ  ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩ እድል የሰጠ ብቸኛው ክልል ነው ብለዋል፡፡

የአማራ ህዝብ ለመንግስት ስርዓት እውቅና የሚሰጥ ህዝብ እንደሆነ የሚናገሩት ዶ/ር አየለ ችግሮች በመንግስት ስርዓት ማዕቀፍ ውስጥ ይፈታሉ ብሎ የሚያምን ህዝብ ነው ብለዋል፡፡አክለውም በክልሉ በርካታ የቱሪስት መስህብ ቦታዎች መኖራቸውን የጠቀሱ ሲሆን የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የጎንደር አብያተ መንግስታት እና የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ሀገራችን በዩኒስኮ ካስመዘገበቻቸው ዘጠኝ ቅርሶች መካከል ሶስቱ ናቸው ብለዋል፡፡በቅርቡ ደግሞ ጣና እና በጣና ውስጥ ያሉ ገዳማት በዩኒስኮ ለመመዝገብ ጫፍ ላይ ደርሰዋል በማለት የአሁኑ ትውልድም አዲስ ታሪክ የሚሰራ፣ የራሱን ታሪክ ፅፎ የሚያልፍ፣ ለችግሮች የማይበገር መሆን አለበት ሲሉ ወጣቶችን መክረዋል፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር የሻምበል አጉማስ “ የወጣትነት የለውጥ አብርሆት ” [መፈተኛ ቤተ ሙከራ] በሚል ርዕስ ለታዳሚዎች ቁልፍ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል፡፡ የለውጥ አብርሆት መነሻ፣ መጓዣ መንገድ እና መዳረሻ አለው የሚሉት ዶ/ር የሻምበል መነሻው ለውጥ ለምን አስፈለገ? የሚል ሲሆን አሁን እንደ ሀገር የገጠመን የሀገር መፍረስ፣የስራ አጥነት፣የስንፍና … አደጋ  የለውጥ አብርሆት መነሻ ነው፤ ይህን ችግር ለመቅረፍ መጓዣ መንገዱ ደግሞ እውነት ላይ መቆም፣ በእውቀት መመላለስ እና በጥበብ ማትረፍ ናቸው ይላሉ፡፡የለውጥ አብርሆት መዳረሻዎችን ሲገልፁ ደግሞ ሰብዓዊ መሆን፣ መክሊታዊ መሆን እና ሳይንሳዊ መሆን ናቸው በማለት ለወጣቶቹ ሳይናሳዊ ትንታኔዎችን ሰጥተዋል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ ከተለያዩ  ብሄር ብሄረሰቦች የመጡ ወጣቶች የየአካባቢያቸውን ባህላዊ ጭፈራዎች ያቀረቡ ሲሆን አዝናኝና አስተማሪ ጭውውት፣ ግጥሞች፣ ፉከራና ሽለላዎች ቀርበው የመድረኩን ተሳታፊዎች ሲያዝናኑ አምሽተዋል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግርማው አሸብር ፕሮግራሙ በተሳካ መንገድ እንዲካሄድ አስተዋፅኦ ለነበራቸው ተባባሪ አካላት ምስጋና አቅርበዋል፡፡አቶ ግርማው አክለውም የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሙኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት መሰል ፕሮግራሞችን በማዘጋጀትና በማስተባበር እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡

ከሰላም ሚኒስቴር ተወክለው ስልጠናውን እያስተባበሩ የሚገኙት አቶ አለማየሁ ለማ የመዝጊያ ንግግር ያቀረቡ ሲሆን የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ስልጠናው ተጀምሮ እስኪያልቅ ኮሚቴ በማዋቀር ላደረጉት ድጋፍ እንዲሁም ለክልሉና ለከተማ አስተዳደሩ የፀጥታና ደህንነት አካላት ሰልጣኞች ያለምንም የፀጥታ ስጋት ስልጠናቸውን እንዲከታተሉ በማድረጋቸው ምስጋና አቅርበዋል፡፡

የዕለቱ የባህል የትውውቅ መድረክ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ህዝብ መዝሙር በጋራ በመዘመር ተጠናቋል፡፡

 

Grade 12 students of BDU-STEM Center, SOS Bahir Dar and Blessed G/Michael Catholic high school students paid a visit to various laboratories and workshops of Ethiopian Institute of Textile and Fashion Technology (EITEX), BIT (Bahir Dar Institute of Technology), EMTI (Ethiopian Maritime Training Institute) and courts of Sport Academy.

 

The visit was organized as part of the year long Diamond Jubilee celebration of Bahir Dar University. During their visit, students were briefed about the history of the university and its present status by Tamiru Delelegn, Alumni Affairs Coordinator of the University. Besides, inspirational stories of its notable alumni were also imparted to the high school seniors.

 

A similar event is planned to be organized by the exhibition committee of the anniversary celebration on monthly basis for similar groups of students from other secondary schools in the city.

The 3rd Annual Sports Festival of Bahir Dar Correction Facility commences
The 3rd Annual Sports Festival of Bahir Dar Correction Facility started today. The festival was organized by the Sport Academy of Bahir Dar university in association with the City's Correction Facility.
During its 3rd annual opening ceremony, the administrator of the facility Commander Abraham Tesfa expressed his deepest gratitude to the City's municipality for improving the quality of the playing grounds and the university's Sport Academy for maintaining its commitment in organizing the annual sport festival.
The festival's organizing team leader, Ato Daniel Getinet from Sport Academy, BDU has forwarded his recognition to individuals & organizations who sponsored the event covering cost of sport kits.
Besides, he presented his appreciation for the inmates for their discipline and the facility for the keen support in hosting the event each year.
Dr. Gashaw Tessema, Vice Dean of the Academy's Research and Community Service Office, stressed the importance of building the youth mentally, physically, socially and emotionally during their correction periods in the facility and reiterated his office's commitment to its realization.
Following the inaugrative speeches, friendly volleyball matches were played between BDU's Business and Economics College and the Facility's best team that lifted the inmates trophy cup. Moreover, rope pulling (Tug of war) competition was held between Zone 1 & zone 2 inmates in which the latter became triumphant. The last match of the opening day ended when Zone 5 beat Zone 4 inmates 3-0 in soccer.

Daniel Mebrhatu founder and owner of Dan-Technocraft company that specialized in the production of escalators and elevator is seen standing right with a hat along with his classmate  Engineer Wubishet Hailu founder and owner of WATT Electromechanical and Pile foundation and Water Well Drilling Enterprise.They both belonged to Electrical Technology graduates of 1965 E.C. Technologist Daniel Mebrhatu was the first of Poly Technic Institute/PTI/ graduates to be an entrepreneur starting with curving letter templates for offices of the Ministry of Education and remain being unemployed by any  company other than developing his own. Engineer Wubishet started his business life being employed with 100 birr  in a governmental company during summer breaks right before joining PTI as a freshman. He managed to buy his first employing company 25 years later, during privatization periods of the late 1980s.

Pages