
Latest News
Teacher Abeba Gela who was class of 1981 and has been serving her country for the past four decades as a teacher and in different administrative capacities and her husband Mr. Birara Ayenew handed over 104 collection of books to Bahir Dar University in the presence of the president of the University, Dr. Firew Tegegne.
Anniversary Memories:
The first batch of Bahir Dar Poly Technic Institute students graduated on Sene 25, 1959 E.C in the presence of Emperor Haileselassie, Ambassador Leonid Teplov (USSR Ambassador to Ethiopia) and other dignitaries like Crown Prince Assfaw Wossen, Prince Imiru Haileselassie, Prince Wossen Seged Mekonnen, Commander Iskinder Desta (Vice commander of Navy), Lij Kassa Woldemariam (President of Haileselassie I University), Akaleworq Habtewold (Minister of Education and Fine Arts), Million Neqiniq (Vice Minister of Education and Fine Arts), Ambassador Yilma Deressa (Minister of Finance), Dr.Haile Giorgis Worqineh (Vice Minister of Labor), and Tsehafe Tizaz Tefera-Worq Kidanewolde (Minister of Palace).
Among the 232 students admitted as freshmen, only 151 managed to complete their studies of whom Tesfaye Biftu, now Professor, seen below in the picture receiving his diploma from H.I.M Haileselassie, completed top from his Industrial Chemistry program and received gold medal.
The professor has became the most influential medicinal chemist in he USA at present. He was the program lead and key innovator in the discovery of 12 drug candidates including Marizev™, the Once Weekly DPP-4 Inhibitor anti-diabetic agent, and key player in the Januvia™ project which has a total sales over 70 billion since its introduction in 2006. He has more than 95 patents registered in his name.
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ተቋም የቆዳና የአልባሳት ምርቶችን ለኤግዚቪሽን አቀረበ
******************************************************************
በባሕር ዳር ከተማ አለ በጅምላ ግቢ በተዘጋጀው የትንሳኤ እና የኢድ ዋዜማ የንግድ ትርኢትና ባዛር ላይ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ተቋም በተማሪዎች ዲዛይን የተደረጉ የቆዳና የአልባሳት ውጤቶችን ለእይታ አቅርቧል፡፡
በኤግዚቪሽኑም ከቆዳና ከጨርቃ ጨርቅ የተሰሩ ጃኬቶች፣ ጫማዎች፣ ቦርሳዎች፣ የህፃናት ማዘያና መሰል ምርቶች ለእይታ ቀርበዋል፡፡
ምርቶቹን ሲመለከቱ ያገኘናቸውና ስለምርቶቹ አጠቃላይ ሁኔታ የጠየቅናቸው ዶ/ር ፀሐይ ነጋ እንደነገሩን አልባሳቱ ለተለያየ ዓላማ እንድንጠቀምባቸው ታስበው በመሰራታቸው ለአጠቃቀም ቀላልና ምቹ ናቸው ብለዋል፡፡ ዲዛይነሮቹ በደንብ ቢታገዙ፣ ቴክኖሎጂው ቢሻሻልና የተሻለ ስልጠና ቢሰጥ ከዚህ የተሻለ ነገር እንደሚሰራ አምናለሁ ብለዋል፡፡ ዶ/ር ፀሐይ አክለውም ምርቶች ላይ ስራ ከመስራታችን አስቀድሞ አመለካከት ላይ መሰራት አለበት ያሉ ሲሆን ምርቶች የትም ሀገር ይመረቱ መታየት ያለበት ጥራታቸው ነው፤ ስለሆነም በሀገራችን ተወዳዳሪ ምርት በማምረት ልክ ህንድን እንደመሰሉ ሀገራት የሀገራችንን ምርት መጠቀም ይኖርብናል ብለዋል፡፡
ሌላው አስተያየታቸውን የሰጡን አቶ ጌታሁን ስዩም ይባላሉ፡፡ ከባሕር ዳር ከተማ እንደመጡ ነግረውን የተሰሩት ስራዎች በጣም ጥሩዎች መሆናቸውን ገልፀው፤ ሆኖም የኢንዱስትሪ ሽግግር እንዲኖር ዩኒቨርሲቲው ከባለሀብቶች ጋር በጋራ መስራት ይኖርበታል ብለዋል፡፡ አክለውም ተማሪዎችን በሚገባ ማብቃትና ትልልቅ ማሽኖችን መጠቀምም ስራውን የበለጠ ለማዘመን ያግዛል ብለዋል፡፡
ምርቶቹን ለተመልካቾች በማቅረብ የማስተዋወቅ ስራ እየሰሩ ያገኘናቸው ወ/ሮ ኑኑሸት ምትኩ ህብረተሰቡ ጥሩ አስተያየት እየሰጠ መሆኑን ነግረውናል፡፡ ይሁን እንጂ ምርቶቹ ለሽያጭ መቅረብ እንዳለባቸው ብዙ አስተያየት ሰጭዎች እንደነገሯቸው አክለው ገልፀውልናል፡፡
‹‹የተማሪዎችን ሁለንተናዊ ዕድገት በማረጋገጥ ጤናማ እና አምራች ዜጋን መፍጠር ቀዳሚ ተግባራችን ነው›› አቶ ኤርሚያስ ዘውዱ የሆፕ ፎር ኢትዮጵያ መስራችና ስራ አስፈፃሚ
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ከሆፕ ፎር ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ውስጥ በሚገኙ 24 ትምህርት ቤቶች (ከኬጅ እስከ መሰናዶ ትምህርት ቤት) ከሚተገብራቸው 5 ዘርፎች የተማሪዎች የጤና መረጃ አያያዝ ስልጠና ለነርሶች መስጠት ጀመረ፡፡
በስልጠና ማስጀመሪያው ላይ የተገኙት የሆፕ ፎር ኢትዮጵያ መስራችና ስራ አስፈፃሚ አቶ ኤርሚያስ ዘውዱ ባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ውስጥ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ድርጅቱ የሚያከናውናቸው ተግባራት ንፅህና አጠባበቅ ፕሮቶኮል፣ በትምህርት ቤት የጤና አገልግሎት አቅርቦት፣ በትምህርት ቤት ቀጣይነት ያለው የተመጣጠነ የምግብ ፕሮግራም፣ በትምህርት ቤት የስፖርት መገልገያዎች እና ቁሳቁሶች ግንባታና አቅርቦት፣ በትምህርት ቤት የአትሌቲክስ ስልጠና እና ልማት ፕሮግራሞች እንደሆኑ ገልፀዋል፡፡
አቶ ኤርሚያስ ፕሮግራሙ በከተማው በሞዴልነት በተመረጡ የጣና ሐይቅ 2ኛ ደረጃ መሰናዶ እና የጠይማ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደሚጀምር ተናግረዋል፡፡ በዚህም ትምህርት ቤቶችን ምቹ የትምህርት አካባቢ በማድረግ ጤናማ እና አምራች ዜጋን መፍጠር እንችላለን ብለዋል፡፡
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የስፖርት አካዳሚ ዲን ዶ/ር ዳኛቸው ንግሩ በበኩላቸው ከሆፕ ፎር ኢትዮጵያ ጋር የአምስት ዓመት መርሃ ግብር ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መገባቱን አውስተዋል፡፡ ለዚህም ፕሮግራም መሳለጥ አስተዋጾ ያደረጉትን የዩኒቨርሲቲውን ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ፕሬዝዳንት ፅ/ቤት፣ የአባይ ማዶ አዲስ አለም ሆስፒታል፣ ለባሕር ዳር ጤና መምሪያ፣ ለኦርቤት ሄልዝ እና አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ምስጋቸውን አቅርበዋል፡፡
የጤና መረጃ አያያዝ ስልጠና ለነርሶች እየሰጡ የሚገኙት የ Orbit Health Domain Expert ዶ/ር ዳኛቸው የዛሬው ስልጠና የሚያተኩረው የተማሪዎች ጤና መመዝገቢያ ፕሮግራም ውጤታማ ለማድረግ ነርሶች በቴክኖሎጅ እየታገዙ ተማሪ ቤት እና ሆስፒታል በቅንጅት የሚሰሩበት ነው ብለዋል፡፡
ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ
Wisdom at the source of Blue Nile
ለተጨማሪ መረጃዎች፡-
Facebook https://www.facebook.com/bduethiopia
YouTube https://www.youtube.com/@bduethiopia
Instagram www.instagram.com/bduethiopia
TikTok https://www.tiktok.com/@bduethiopia
Telegram https://t.me/bduethiopia
Twitter https://twitter.com/bduethiopia
LinkedIn http://www.linkedin.com/school/bduethiopia
Website https://bdu.edu.et/
#bdu60th_anniversary
ኢትዮጵያ በዩኒስኮ ካስመዘገበቻቸው ዘጠኝ ቅርሶች መካከል ሶስቱ በአማራ ክልል እንደሚገኙ ተገለፀ
የሰላም ሚኒስቴር ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የሚያሰለጥናቸው የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች የባህል ትውውቅ መድረክ በስራ አመራር አካዳሚ አዳራሽ በድምቀት ተካሂዷል፡፡
በትውውቅ መድረኩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አየለ አናውጤ ለመድረኩ ተሳታፊዎች እንደገለፁት አማራ ክልል በርካታ ብሄር ብሄረሰቦችን የያዘ፤ ከ20 በላይ ዞኖችና ሪጂኦ ፖሊታን ከተሞች የተዋቀረ፤ በርካታ ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊ፣ ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ ቅርሶችን የያዘ ክልል ነው ብለዋል፡፡ክልሉ ስያሜው የአማራ ክልል ይሁን እንጂ የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦችን አቅፎ የያዘ ክልል ነው የሚሉት ዶ/ር አየለ ለበርካታ ብሄር ብሄረሰቦች እውቅና በመስጠት የመንግስታዊ መዋቅሩ አካል ያደረገ ክልል ነው ብለዋል፡፡ለዚህም ለኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን፣ ለአዊ ብሄረሰብ ዞን፣ ለዋገኸምራ ብሄረሰብ ዞን እና ለአርጎባ ልዩ ወረዳ ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩ እድል የሰጠ ብቸኛው ክልል ነው ብለዋል፡፡
የአማራ ህዝብ ለመንግስት ስርዓት እውቅና የሚሰጥ ህዝብ እንደሆነ የሚናገሩት ዶ/ር አየለ ችግሮች በመንግስት ስርዓት ማዕቀፍ ውስጥ ይፈታሉ ብሎ የሚያምን ህዝብ ነው ብለዋል፡፡አክለውም በክልሉ በርካታ የቱሪስት መስህብ ቦታዎች መኖራቸውን የጠቀሱ ሲሆን የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የጎንደር አብያተ መንግስታት እና የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ሀገራችን በዩኒስኮ ካስመዘገበቻቸው ዘጠኝ ቅርሶች መካከል ሶስቱ ናቸው ብለዋል፡፡በቅርቡ ደግሞ ጣና እና በጣና ውስጥ ያሉ ገዳማት በዩኒስኮ ለመመዝገብ ጫፍ ላይ ደርሰዋል በማለት የአሁኑ ትውልድም አዲስ ታሪክ የሚሰራ፣ የራሱን ታሪክ ፅፎ የሚያልፍ፣ ለችግሮች የማይበገር መሆን አለበት ሲሉ ወጣቶችን መክረዋል፡፡
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር የሻምበል አጉማስ “ የወጣትነት የለውጥ አብርሆት ” [መፈተኛ ቤተ ሙከራ] በሚል ርዕስ ለታዳሚዎች ቁልፍ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል፡፡ የለውጥ አብርሆት መነሻ፣ መጓዣ መንገድ እና መዳረሻ አለው የሚሉት ዶ/ር የሻምበል መነሻው ለውጥ ለምን አስፈለገ? የሚል ሲሆን አሁን እንደ ሀገር የገጠመን የሀገር መፍረስ፣የስራ አጥነት፣የስንፍና … አደጋ የለውጥ አብርሆት መነሻ ነው፤ ይህን ችግር ለመቅረፍ መጓዣ መንገዱ ደግሞ እውነት ላይ መቆም፣ በእውቀት መመላለስ እና በጥበብ ማትረፍ ናቸው ይላሉ፡፡የለውጥ አብርሆት መዳረሻዎችን ሲገልፁ ደግሞ ሰብዓዊ መሆን፣ መክሊታዊ መሆን እና ሳይንሳዊ መሆን ናቸው በማለት ለወጣቶቹ ሳይናሳዊ ትንታኔዎችን ሰጥተዋል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ ከተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦች የመጡ ወጣቶች የየአካባቢያቸውን ባህላዊ ጭፈራዎች ያቀረቡ ሲሆን አዝናኝና አስተማሪ ጭውውት፣ ግጥሞች፣ ፉከራና ሽለላዎች ቀርበው የመድረኩን ተሳታፊዎች ሲያዝናኑ አምሽተዋል፡፡
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግርማው አሸብር ፕሮግራሙ በተሳካ መንገድ እንዲካሄድ አስተዋፅኦ ለነበራቸው ተባባሪ አካላት ምስጋና አቅርበዋል፡፡አቶ ግርማው አክለውም የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሙኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት መሰል ፕሮግራሞችን በማዘጋጀትና በማስተባበር እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
ከሰላም ሚኒስቴር ተወክለው ስልጠናውን እያስተባበሩ የሚገኙት አቶ አለማየሁ ለማ የመዝጊያ ንግግር ያቀረቡ ሲሆን የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ስልጠናው ተጀምሮ እስኪያልቅ ኮሚቴ በማዋቀር ላደረጉት ድጋፍ እንዲሁም ለክልሉና ለከተማ አስተዳደሩ የፀጥታና ደህንነት አካላት ሰልጣኞች ያለምንም የፀጥታ ስጋት ስልጠናቸውን እንዲከታተሉ በማድረጋቸው ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የዕለቱ የባህል የትውውቅ መድረክ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ህዝብ መዝሙር በጋራ በመዘመር ተጠናቋል፡፡
Grade 12 students of BDU-STEM Center, SOS Bahir Dar and Blessed G/Michael Catholic high school students paid a visit to various laboratories and workshops of Ethiopian Institute of Textile and Fashion Technology (EITEX), BIT (Bahir Dar Institute of Technology), EMTI (Ethiopian Maritime Training Institute) and courts of Sport Academy.
The visit was organized as part of the year long Diamond Jubilee celebration of Bahir Dar University. During their visit, students were briefed about the history of the university and its present status by Tamiru Delelegn, Alumni Affairs Coordinator of the University. Besides, inspirational stories of its notable alumni were also imparted to the high school seniors.
A similar event is planned to be organized by the exhibition committee of the anniversary celebration on monthly basis for similar groups of students from other secondary schools in the city.
Daniel Mebrhatu founder and owner of Dan-Technocraft company that specialized in the production of escalators and elevator is seen standing right with a hat along with his classmate Engineer Wubishet Hailu founder and owner of WATT Electromechanical and Pile foundation and Water Well Drilling Enterprise.They both belonged to Electrical Technology graduates of 1965 E.C. Technologist Daniel Mebrhatu was the first of Poly Technic Institute/PTI/ graduates to be an entrepreneur starting with curving letter templates for offices of the Ministry of Education and remain being unemployed by any company other than developing his own. Engineer Wubishet started his business life being employed with 100 birr in a governmental company during summer breaks right before joining PTI as a freshman. He managed to buy his first employing company 25 years later, during privatization periods of the late 1980s.