የስርዓተ ትምህርት ክለሳ

የገጠር ልማት ት/ክፍል በድህረ ምረቃና በሶስተኛ ዲግሪ አዳዲስ ፕሮግራሞችን ለመክፈት የስርዓተ ትምህርት ክለሳ አካሄደ
በሙሉጎጃም አንዱዓለም

በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ስር የሚገኘው የገጠር ልማት ት/ክፍል PhD in Rural Development (የሶስተኛ ዲግሪ በገጠር ልማት) እና MSc in Agricultural Extension and Innovation (የሁለተኛ ዲግሪ በግብርና ኤክስቴንሽን ኢኖቬሺን) አዳዲስ ፕሮግራሞች ለመክፈት በኮሌጁ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የስርዓተ ትምህርት ክለሳ አካሂዷል፡፡

የኮሌጁ መምህርና ተመራማሪ ዶ/ር ግርማቸው ስራው በግብርና ኤክስቴንሽን ኢኖቬሺን የሁለተኛ ዲግሪ የስርዓተ ትምህርት ረቂቁን አቅርበው እንዲገመገም ተደርጓል፡፡ ዶ/ር ግርማቸው የትምህርት ፕሮግራሙን መከፈት አስፈላጊነት ሲያስረዱ እንደተናገሩት ት/ክፍሉ በመጀመሪያ ዲግሪ ደረጃ በግብርና ኤክስቴንሽን ኢኖቬሺን ተማሪዎችን እያሰለጠነ ቢሆንም በሀገሪቱ በሙያው ተሰማርተው ያሉት ሙያተኞች ቁጥራቸው አናሳ ከመሆኑም በላይ የክህሎት ውስንነት ስለሚስተዋልና በሌሎች ሙያተኞች ስራው እየተሰራ በመሆኑ እንዲሁም በአገር አቀፍ ደረጃ ፕሮግራሙ የመጀመሪያ መሆኑ መከፈቱ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ የሁለቱም ካሪኩለም ረቂቅ ቀርቦ በገምጋሚ እንግዶችና ታዳሚዎች አስተያየቶች ቀርበው ከአቅራቢዎችና በፕሮግራሙ ተሳታፊ በሚሆኑ መምህራን ግብረ-መልስ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል፡፡