ስጦታ ተበረከተ

ኮሌጁ ለዝሆኔ በሽታ ተጠቂዎች የአልባሳት ስጦታ አበረከተ

በሙሉጎጃም አንዱአለም

የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለደቡብ አቸፈር ወረዳ የዝሆኔ በሽታ ተጠቂዎች የጫማ ስጦታ በማበርከት የማህበረሰብ አገልግሎት ስራ አከናውኗል::

የኮሌጁ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ተጠሪ ዶ/ር ወንድማገኝ እምቢአለ ማህበሩ እንደ ኢትዮጲያ አቆጣጠር በ2004 ዓ.ም የተመሰረተና ከ400 በላይ አባላት እዳሉት ገልፀው ከአሁን በፊት በርካታ የበሽታው ተጠቂዎች ተከታታይ የህክምና አገልግሎት ስለተሰጣቸው ዘላቂ ፈውስ ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡

በርክክቡ ስነ-ስርዓትም የማህበሩ ሰብሳቢ አቶ ዳኛው ዋሴ፣በሂሳብ ሹምነት እያገለግሉት የሚገኙት አቶ ስሜነህ ደርሶ እና የኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ደረበ ነጋ በወረዳው ጤና ጣቢያ ቅጥር ግቢ ውስጥ ከዶ/ር ወንድማገኝ እጅ  የጫማ ስጦታውን ተቀብለዋል፡፡

ስጦታውን የተረከቡት የኮሚቴ አባላት ከአሁን በፊት በዶ/ር ወንድማገኝ በኩል ከፍተኛ የህክምና አገልግሎት አግኝተው ከበሽታቸው መፈወሳቸውንና በየጊዜው የጫማ ስጦታ እየተደረገላቸው በመሆኑ የማህበሩ አባላት በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ በአንክሮ ተናግረዋል፡፡