የመምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ስልጠና

ለመምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ዳይሬክቶሬት ለዩኒቨርሲቲው መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች በ Leadership and Change Management ፣ Statistical Package for Social Science ( SPSS )፣ Payton Programming  እና በግዢና ንብረት አስተዳደር የሙያ ዘርፎች  ስልጠና ሰጠ ::

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ወርቁ አበበ እንደተናገሩት በአስተዳደር ሰራተኞች በኩል የዝቅተኛና የመካከለኛ አመራሮችን በራስ የመወሰን አቅማቸዉን ለማጎልበት ያመች ዘንድ በማዕከላዊና በተለያዩ ግቢዎች ለሚገኙ አመራሮች በ Leadership and Change Management ዙርያ ለ4 ቀናት ፣በግዢና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በኩል ደግሞ በሁሉም ግቢ ለሚገኙ የንብረት አስተዳደር ሰራተኞች ንብረትን በሲስተም እንዴት ማስተዳደርና መጠቀም እንደሚቻል በተግባር የታገዘ ለ2 ቀናት ስልጠና መሰጠቱን ገልፀውልናል፡፡

አያይዘውም የስልጠና ዳይሬክቶሬቱ በዘንዘልማ ግቢ ለሚገኙ መምህራን የምርምር ስራቸዉን በተገቢዉ ለመስራት ያመቻቸዉ ዘንድ ከስታትስቲክስ ትምህርት ክፍል አሰልጣኞችን በማስመጣት Statistical Package for Social Science ( SPSS ) ለ 5 ተከታታይ ቀናት ስልጠና የተሰጣቸዉ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በሂሳብ ትምህርት ክፍል Payton Programming ስልጠና ለተከታታይ አምስት ቀናት ስልጠና ተሰጥቷል ብለዋል ፡፡

በአጠቃላይ በአሁኑ ሰዓት በሁሉም ዘርፍ ከ 03-09/02/2013 ዓ/ም ድረስ 154 የሚሆኑ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ስልጠናዉን በተገቢዉ መንገድ ተከታትለዉ ማጠናቀቃቸዉን የዩኒቨርሲቲዉ የስልጠና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ወርቁ አበበ ገልጸዋል፡፡