የሐኪሞች ሙሉ ልብስ ማምረቻ ጉብኝት

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን፣ የሐኪሞች ሙሉ ልብስ ማምረቻን ጎበኙ።

........................ ........................ ................................................

 

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሪት ሔራን ገርባ ከሌሎች የመስሪያ ቤቱ ባለስልጣናት ጋር በመሆን በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፣ የኢትዮጵያ ቴክስታይል እና ፍሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ስር የሚገኘውን የሐኪሞች ሙሉ ልብስ (Coverall) ማምረቻና ማስተማሪያ ፍብሪካ ጎብኝተዋል። በጉብኝቱም  በተሰጠው የጥራት ዕውቅና መሰረት እያመረተ መሆኑንና በቀን እስከ 400 የሐኪሞች ሙሉ ልብስ የማምረት አቅም እንዳለው መረዳት ተችሏል። በአሁኑ ወቅትም የተለያዩ የመንግስት እና የግል ሆስፒታሎች ምርቱን ወስደው እየተጠቀሙ ሲሆን፣ እንዲመረትላቸው ጥያቄ ያቀረቡ እንዳሉም ማወቅ ተችሏል።

 

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሪት ሔራን ገርባ በተቋሙ እየተሰሩ ያሉ  ስራዎች አበረታችና ለሌሎች ተምሳሌት መሆናቸውን ገልፀው፣ወደፊትም መስሪያ ቤቱ ማንኛውም ሙያዊ እገዛ እንደሚደረግላቸውና፤ ሌሎች በላብራቶሪ ደረጃ ላይ ያሉ ምርቶችም ለሀገር ጠቃሚና የውጭ ግዥ የሚያስቀር መሆኑን ገልፀው፣ መስፈርቶችን ሲያሟሉ ለመስሪያ ቤቱ የኢትዮጵያ ቴክስታይል እና ፍሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፣ የእውቅና ጥያቄ ማቅረብ እንደሚችል ገልፀዋል።