የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የግምገማና ክትትል

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የግምገማና ክትትል ቡድን ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ለመቀበል እየሰራ ያለውን የቅድመ ዝግጅት ስራ ገመገመ

-----------------------------------------------------------------------------------------------------

በሙሉጌታ ዘለቀ

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ኮቪድ-19ን በመከላከል ትምህርት ለመጀመር  ዩኒቨርሲቲዎች ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ በሰጠው አቅጣጫ መሰረት የባሕር ዳር  ዩኒቨርሲቲ  የኮቪድ 19 ኘሮቶኮልን ተከትሎ የተማሪዎች መኝታ ቤት፣ የመመገቢያ አዳራሾች፣ ቤተ መጻሕፍት፣ ቤተ ሙከራዎች እና የተማሪዎች መዝናኛዎች በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት የተሰሩ ስራዎችን ገምግሟል፡፡

 

እንደሚታወቀው በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሳለፍነው የትምህርት ዘመን በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ተማሪዎቻችን ከትምህርት ገበታቸው ተለይተው ቆይተዋል፡፡ በያዝነው ዓመት ወረርሽኙን በመከላከል ዩኒቨርሲቲዎች  ትምህርት ለማስቀጠል የሚያሰችል ደረጃ ላይ መሆናቸውን  ከሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስተር የተላከ የሱፐርቪዥን ቡድን እያረጋገጠ ይገኛል፡፡

 

 በመሆኑም የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሰራተኞች የኮረና ቫይረስ ቅድመ መከላከል ስልጠናና ምርመራ ማድረጋቸውን፣ ተማሪዎች ሲገቡ የሚኖራቸው መስተጋብር ምን መምሰል እንዳለበት ዩኒቨርሲቲው በስምንቱም ግቢዎች ያደረገውን ቅድመ ዝግጅትና የተሰሩ ስራዎችን  የግምገማና ክትትል ቡድኑ ተመልክቷል፡፡