የመንጃ ፍቃድ መረጃ አያያዝ ዘዴ

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የሰራውን የመንጃ ፍቃድ መረጃ  አያያዝ ዘዴ( Driving License Information Management System) አስመረቀ

በወንዳለ ድረስ

በኢንስቲትዩቱ የዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ  ትስስር እና ማህበረሰብ  አገልግሎት  ጽ/ቤት ድጋፍ  የማህበረሰቡን  ችግር

ለመፍታት የተሰራውን Driving License Information Management System ቴክኖሎጂ ባለድርሻ

አካላት በተገኙበት መስከረም 30/2013 ዓ.ም አስመርቋል፡፡

 

በምረቃ ስነ ስርዓቱ  አቶ ቴዎድሮስ ጌራ በኤሌክትሪካል  እና ኮምፒዩተር ኢንጂነሪንግ  ፋኩልቲ  ዲን  በመክፈቻ

ንግግራቸው ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር፣ ማህበረሰብ አገልግሎትና ምርምር ተልኮዎች ባሻገር በተለያየ

ወቅት ዘርፈ ብዙ ቴክኖሎጂዎችን በማበልፀግ ለተለያዩ ተቋማት አገልግሎት እንዲሰጡ  ማስረከቡን  አስታውሰዋል፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴከኖሎጂ ኢንስቲትዩት ኤሌክትሪካል እና ኮምፒዩተር ኢንጂነሪንግ ፋኩልቲ የሚሰሩት አቶ አማረ ካሳው ቴክኖሎጂውን ሲያስተዋውቁ እንደተናገሩት የመረጃ አያያዝ ዘዴው  የመንግስት  ገቢን  ለማሻሻል፣  የትራፊክ  አደጋን  ለመቀነስ ፣ የተቋሙን አፈፃፀም  ለማሻሻል፣  የሥራ  አፈፃፀሙን  ለማስተዳደር  እና  ለመቆጣጠር የራሱን እገዛ እንደሚያደርግ ገልፀው ቴክኖሎጂው የሥልጠና  ተቋማቱን የሚደግፍና ለአሽከርካሪዎች አገልግሎቱን ቀላል በማድረግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፆ እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡

 

በመጨረሻም የአብክመ መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ውቤ አጥናፉ እና የባህር ዳር ከተማ መንገድ

ትራንስፖርት ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ወዳጀ  የመንጃ ፍቃድ ስርዓቱ በሚሻሻልበት መንገድ ዙሪያ በክልሉ ከሚገኙ

የዞን መንገድ ትራንስፖርት ባለሙያዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡