Latest News

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በጤናው ዘርፍ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ
**************************************************************************
[ህዳር 10/2015 ዓ.ም፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ] የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በጤናው ዘርፍ በሰባት ትምህርት ክፍሎች ለ9ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን 57 የስፔሻሊቲ ሐኪሞች 13 የማስትርስ ድግሪ እና 182 በመጀመሪያ ድግሪ በድምሩ 252 ተማሪዎችን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ በተገኙበት በጥበብ ህንፃ የመስብሰቢያ አዳራሽ በድምቀት አስመርቋል፡፡
በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ሽፈራው ተመራቂ ተማሪዎች ባለፉት ዓመታት ሀገራችንና መላው ዓለም ያሳለፈውን ከባድ የፈተና ግዜ አልፋችሁ፣ የእናንተ እና የወላጆቻችሁ ከፍተኛ የትግስት ውጤት ለሆነው የምረቃ ቀናችሁ እንኳን አደረሳችሁ ብለዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ የምርምር ዩኒቨርሲቲ የመሆን ራዕዩን በማስቀመጥ ለምርምር እና ማሕበረሰብ አገልግሎት ዘርፉ ትኩረት ሰጥቶ እሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዶ/ር ተስፋዬ አክለውም ዩኒቨርሲቲው የምርምር ዩኒቨርሲቲ የመሆን ራዕዩ እንዲሳካ በትምህርት ጥራት ማሳደግ፣ በምርምር፣ በማህበረሰብ አገልግሎት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎች ውስጥ በመሳተፍ የኩራት አምባሳደር እንድትሆኑ ሲሉ ለተመራቂዎች መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
በተማሪዎች ምረቃ ላይ የዕለቱ የክብር እንግዳ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ በንግግራቸው ለተመራቂዎች በዛሬው እለት የህክም ትምህርታችሁን የጨረሳችሁበት ሳይሆን ይልቁንም የህክምና ትምህርታችሁን መሰረታዊ ክህሎቶችን ይዛችሁ የህዝባችሁን ጤና ለመጠበቅ ታላቅ ሃላፊነትን በመቀበል የሂዎት ዘመን የህክምና ትምህርት ቤት የምትቀላቀሉበት እና ሌላውን የህይወት ምዕራፍ የምትጀምሩበት ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ዛሬ የምትቀላቀሉት ሙያ የህይወት ዘመን ትምህርት እና ፍላጎትን የሚጠይቅ እንዲሁም የአውንታዊ ማህበረሰብ ግንኙነት የሚሻ በመሆኑ በቀጣዩ የአገልግሎት ጊዜያችሁ ከተለያዩ የሙያው አጋሮች ጋር በመሆን የማህበረሰቡን ጤና ለመጠበቅ እና ለማጎልበት ተግታችሁ እንድትሰሩ ሲሉ ለተመራቂ ተማሪዎች የአደራ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ አክለውም የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ በጤናው ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ዘርፍ በሰውሃይል ልማቱ ላይ እያበረከተ ያለውን ጉልህ አስተዋፆ እና በተለይም ለትምህርት ጥራት ለአካባቢ ልማት ምቹ አረንጓዴ ከባቢን የመፍጠር ጥረት አድንቀው በቀጣይ ዘመኑን የዋጄ ቴክኖሎጂዎችን ጭምር በመጠቀም የመማር ማስተማር ስራውን በማዘመን ለትምህርት ጥራት የሰጣችሁትን ትኩረት አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂ ተማሪዎች የሜዳሊያ እና የእውቅና የምስክር ወረቀት መርሃ ግብር ተካሂዷል፡፡ በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ የሙሉዓለም የባህል ቡድን ባህላዊ እና ዘመናዊ ሙዚቃዎችን በማቅረብ የፕሮግራሙ ታዳሚዎችን አዝናንቷል፡፡
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
-------------------------------------
``ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ``
``Wisdom at the source of Blue Nile``
Thank you for visiting, inviting and sharing our Pages!
Thank you for your likes and comments too!
ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

The 7th annual national seminar is underway

Institute of disaster risk management and food security studies, BDU, is holding its 7th annual national educational conference. In the seminar, about 14 research papers are presented. Director of the Institute Dr. Mintesnot Azene, Ayatam Fentahun, National Project Manager for EU- Strengthening Decentralization of DRM in Ethiopia Project, BDU members of top management, researchers from Bahir Dar and other Universities and teachers among others are participating in the seminar.

The Faculty of Humanities holds the first seminar of the new academic year 

It has become an academic routine for the Faculty of Humanities BDU to hold academic seminars since some more than a decade now. Many seminars with diversified topics from all the fields of studies in the faculty have been held. Today's paper was presented by Tewodros Yideg from the Department of Theatrical Arts on the title: “ሴትነት፣እምቢተኝነትና ነፃነት፡- የቃቄ ውርድዎት ትውፊታዊ ተውኔት ሂሳዊ ግምገማ” and moderated by Dr. Sintaheyu Degu, Faculty’s V/Dean for postgraduate, research and community services.

The faculty has schedule Friday afternoons for seminars; subsequently, classes are not conducted for this purpose. This undertaking, in addition to becoming a platform for academic discussions, it has been benefiting graduate program students to exercise academic presentations of their theses and dissertations. Similar academic discourses are very important in our university as we strive towards becoming one of the premium research universities in Africa. Based on questions and comments from the audience, reflections were made.

 

In the seminar, the dean, vice deans, teachers, graduate and under graduate students participated.

ብሔራዊ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰልጣኞች ከተመዋን ማፅዳት ጀመሩ

ህዳር 4/2015 ዓ/ም (ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ) 

በሰላም ሚኒስቴር እና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትብብር ‹‹በጎነት ለአብሮነት›› በሚል መሪ ሃሳብ ከሁሉም ክልሎች ለተውጣጡ ከ2000 በላይ ወጣቶች ለ33 ቀናት የሚቆይ ስልጠና  በባሕር ዳር  ዩኒቨርሲቲ እየተሰጠ ሲሆን በዛሬው እለት ከዋናው  ፔዳ  ግቢ እስከ  ዊዝደም  አደባባይ  የሚገኘውን  መንገድ ከበላይ ዘለቀ ክፍለ ከተማ ጋር በመቀናጀት የመጀመሪያ የሆነውን  ብሔራዊ  የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራ ጀምረዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አስተባባሪ አቶ ዘውዴ ኤጄርማ በጎ ፈቃድ ሰጭዎቹ ከሰኞ እስከ ቅዳሜ በመደበኛ ስልጠና የወሰዱትን ከከተማው ማህበረሰብ ጋር በመሆን ዛሬ የበጎ ፈቃድ ስራን በፅዳት ጀምረዋል፡፡ ወጣቶቹ በአገሪቱ ከሚገኙ ሁሉም ክልሎች የተውጣጡ ሲሆኑ ስልጠናውን ለ33  ቀናት  ከወሰዱ በኋላ ከሚኖሩበት አካባቢ ራቅ ወዳለ ቦታ ተመድበው ለ10 ወር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት  እንዲሰጡ  ይደረጋል፡፡  የዛሬው  የፅዳት  ስራም  ለቀጣይ ስራዎች  መነሳሳትን  ይፈጥርላቸዋል ብለዋል፡፡

አቶ ዘውዴ ስለዓላማው ሲናገሩ ከህብረተሰቡ ጋር ያለውን ትስስር ለማጠናከር፣ አካባቢውን  ማፅዳትና አቅመ ደካሞችን መርዳት፤ በጎነትን ማነሳሳት እና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተሸረሸረ የመጣውን አንድነት ማጠናከር ነው ብለዋል፡፡

በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የበላይ ዘለቀ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጊዜው ታከለ  በበኩላቸው ከሰላም ሚኒስቴር የመጡ የበጎ ፈቃድ የሚሰጡ  ወጣቶች ዛሬ  የፅዳት ስራ  የጀመሩባት  ከተማ በተፈጥሮ የታደለች፣ ብዙ ታሪካዊ ቦታዎች በሚገኙበት፣ የአማራ ባህልና እሴት  የሚንፀባረቅባት  ባሕር  ዳር ከተማ ናት፡፡  በተፈጥሮ ውብ ከመሆኗ  ባሻገር ነዋሪዎቿ  በየጊዜው  አካባቢያቸውን በማፅዳት፤ ችግኞችን በመትከልና በመንከባከብ  ለኑሮ እና ለቱሪስት  ምቹ እንዲሆን እየሰሩ የሚገኙ ሲሆን ዛሬም ይህን ለማስቀጠል ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር  እየሰራን እንገኛለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የበጎ ፍቃድ አገልግሎቱን ለመስጠት ከደብረ ማርቆስ ከተማ የመጣው ወጣት ወንዳለ ይሄነው  እንደተናገረው በሳምንቱ የስልጠና ቆይታችን ስለ ህይወት ያለንን አስተሳሰብ፤ ትናንትናችን በደንብእንድናይ፣ ዛሬአችን ደግሞ በደንብ እንድናመዛዝን አድርጎልናል፡፡ ከዚህ በኋላም ከምንሄድበት  ማህበረሰብ ጋር እንዴት መቆየት እንዳለብን ጥሩ ስንቅ ሆኖናል፡፡ የዛሬውም የበጎ ፍቃድ  አገልግሎት እንደመጀመሪያ ስልጠናውን በተግባር ያየንበት ነው ብለዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ መጨረሻ ለበጎ ፈቃድ ሰልጣኞች መልዕክት ያስተላለፉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲአጠቃላይ ጥራት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር አንዳርጋቸው ሞገስ በጎ ፈቃድ ሰጭዎቹ በቀጣይ ፕሮግራም የተያዘውን ማህበረሰቡን የሚጠቅሙ ማለትም እንቦጭን ማፅዳት  እና የደም መለገስ ተግባራት ላይ እንደሚሳተፉ ተናግረዋል፡፡

 

የኢትዮጵያና የአፍሪካ ቀንድ ታሪክ ሞጁል ላይ አውደጥናት ተካሄደ

*****************************************************************************************************የትምህርት ሚንስቴር ከኢትዮጵያ ታሪክ ባለሙያዎች ማህበር ጋር በመተባበር የኢትዮጵያና የአፍሪካ ቀንድ ታሪክ በሚል ርዕስ የተዘጋጀውን ሞጁሉ  ለአንደኛ ዓመት የዩኒቨርሲቲ  ተማሪዎች  በሦስት ክሬዲት አወር በኮመን ኮርስ ለመስጠት  የሚያስችለውን  የግንዛቤ ማስጨበጫ አውደጥናት በርካታ የታሪክ ሙሁራን በተገኙበት  በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበብ ሕንፃ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሂዷል፡፡

በምክክር መድረኩ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተከታታይና  ርቀት ትምህርት ፕሮግራም ዳይሬክተር ዶ/ር አበበ ድረስ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከ11 ዓመት በፊት በ2004 ዓ.ም ከሃያ በላይ የሚሆኑ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህራንን በመጋበዝ ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንደ ኮመን ኮርስ እንዲሰጥ የውይይቱ ዋና አጀንዳ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ ወጣቶችን እና ማህበረሰቡን ማንቃት በታሪክ በኩል ያለውን ክፍተት ለመሙላት የታሪክ ትምህርትን በኮመን ኮርስ እንዲሰጥ እና የታሪክ ሙሁራን ማህበር  መመስረት እንደነበረ ጠቅሰው ከ11ዓመት በኋላ ተሳክቶ በማየታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡ እንደ ዶ/ር አበበ ገለፃ ማህበሩ መመስረቱ እና ትምህርቱን በኮመን ኮርስ መሰጠቱ ጥሩ ነገር ሆኖ ቀጣይ ትግበራው ላይ ሊገጥሙ የሚችሉ ችግሮችን ከወዲሁ ሙሁራዊ በሆነ መንገድ ለመፍታት የእለቱ የውይይት መድረክ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ዶ/ር ታዬ ደምሴ የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊ ሳይንስ ፋኩልቲ ዲን በበኩላቸው የታሪክ ትምህርት እንደ ኮመን ኮርስ ሲሰጥ ስድስተኛው ኮርስ መሆኑን ጠቅሰው ኮርሱ ለተማሪዎች በትክክል እና በአግባቡ ተደራሽ እንዲሆን የመምህራን ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ትምህርቱን በሀገር አቀፍ ደረጃ  በኮመን ኮርስ ለመስጠት ረጅም አመታት መውሰዱን እና በጉዳዩ ላይም ብዙ ክርክር እና እሰጣገባ እንደነበረ ጠቅሰው በታሪክ ሙሁራን ማህበር ብርቱ ትግል ለውጤት መብቃቱን በመግለፅ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በጉዳዩ ዙሪያ ያበረከተው አስተዋፃ ከፍተኛ መሆኑን ዶ/ር ታዬ ተናግረዋል፡፡

በምክክር መድረኩ ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህር እና ተመራማሪ የሆኑት ፕ/ር ሹመት ሲሻኝ አጠቃላይ የሞጁሉን አሰጣጥ እና አቀራረቡን በተመለከተ የመነሻ ጥናታዊ ፁሁፍ አቅርበዋል፡፡  የኢትዮጵያ ታሪክ እንደግዴታ ሆኖ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አለመሰጠቱ ሀገራዊ ጉዳት ብቻ ሳይሆን ሙያዊ ጉዳቱ ከፍተኛ መሆኑን በጥናታዊ ፁሁፋቸው አመላክተዋል፡፡ እንደ ፕ/ር ሹመት ገለፃ ያለታሪክ አንድን ሀገር አንድ አድርጎ ማቆየት አስቸጋሪ መሆኑን ጠቅሰው ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የተለያየ ቋንቋ እና ባህል ያለው ህዝብ የዜግነት እና የጋራ ስሜት ሊያዳብር የሚችለው የሀገሪቱን ታሪክ በማስተማር እና በማሳወቅ የጋራ ማድረግ ሲቻል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በመጨረሻም በምክክር መድረኩ ተሳታፊ መምህራን በኩል የታሪክ ትምህርት ላለፉት 30 ዓመታት በተዳከመበት እና ቀድሞ የነበረው ትምህርት ክፍሎች በተወሰነ ደረጃ ትኩረት አጥተው  እና መምህራንም ሌላ የትምህርት መስክ ቀይረው ባለበት ሁኔታ ትውልዱን ወደራሱ ታሪክ እንዲመለስ ለማድረግ ጠንከር ያለ አካሄድ እና የክትትል ስራ እንደሚያስፈልግ ሀሳብ ቀርቧል፡፡ የኢትዮጵያና የአፍሪካ ቀንድ ታሪክ  (History of Ethiopia and the Horn) የሚል ርዕስ ያለው ሞጁሉ በሰባት ምዕራፎች የተከፋፈለና 187 ገጾች የያዘ ሲሆን በአንድ ሴሚስተር ለማዳረስ ከተሰጠው ሰዓት አንፃር ከባድ በመሆኑ ማብሪሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀው ከመድረክ ማብራሪያ እና ገለፃ ተሰጥቶበታል ፡፡    

አሸናፊ አሳታፊ የሰብል ዝርያዎችን የማስፋት ፕሮጀክት አመርቂ ስራ መስራቱ ተገለጸ

*************************************************************************

አሸናፊ አሳታፊ የሰብል ዝርያዎችን የማስፋት ፕሮጀክት (Upscaling Crowdsourced ‘’winner’’ seed varieties project) በፈረንጆች አቆጣጠር ከ2020 ጀምሮ በኢትዮጵያ ውስጥ በአማራ ክልል በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በትግራይ ክልል በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ እና በኦሮሚያ ክልል ሲድ ኢንተርፕራይዝ ጋር በመተባበር አርሶ-አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርግ በምርምር የተገኙ የተሻሻሉ እንዲሁም የአካባቢ የሰብል ዝርያዎችን በቀጥታ ብሎም በተዘዋዋሪ ለአርሶ-አደሮች በማዳረስ ቅድመ ስብሰባ እና ድህረ ምርት አየያዝን ጨምሮ ክትትል በማድረግ ውጤታማ ስራ እየተሰራ መሆኑን ተጠቃሚ አርሷደሮች ተናግረዋል፡፡

የፕሮጀክቱ ዋና ዓላማ የሃገራችን ዋናው የኢኮኖሚ ምሰሶ ለሆነው የግብርናው ዘርፍ ግንባር ቀደም የምርጥ ዘር ተጠቃሚ አርሶ-አደሮች በማምረት ያገኙትን ውጤት ሌሎችም አርሶ-አደሮች እንዲአስተዋዉቁ እና በማካፈል ተጠቃሚ እንዲሆኑ በስፋት መሰራት እና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር፤ በገበያ ተፈላጊና የተሻለ ዋጋ ያላቸውን ምርቶች ለማምረት ግብዓትና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ተደራሽነትን እንዲሁም ጥራትን ማረጋገጥ በትኩረት እና አሳታፊ በሆነ መልኩ መስራት እንደሆነ በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል፡፡

ፕሮጀክቱ በደቡብ ጎንደር ዞን ፋርጣ ወረዳ የሀውዘት ቀበሌ፣አዲስ አለም የዘር ብዜት እና ግብይት ማህበር፣ በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረኤሊያስ ወረዳ የጥጃ ገጠር ቀበሌ የላቀ ማርቆስ የዘር ብዜት እና ግብይት ህብረት ስራ ማህበር፣ በምዕራብ ጎጃም ዞን ቡሬ ዙሪያ ወረዳ በዋድሪ ቀበሌ ሰርተን እንደግ የዘር ብዜት እና ግብይት ህብረት ስራ ማህበር፣በሜጫ ወረዳ ኩድሚ የዘር ብዜት ማህበር እና ሰሜን አቸፈር ወረዳ ሊበን ዳንጉር ቀበሌ ዘልቆ በመግባት ለአርሶ-አደሩ  የተሻሻሉ የዳጉሳ፣የመኮረኒ ስንዴ እና የባቄላ ምርጥ ዘሮችን በማቅረብ የተሸለ ምርት እንዲመረት ማድረጉ ተገልጿል፡፡   

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መምህር እና ተመራማሪ እንዲሁም የፕሮጀክቱ አስተባባሪ የሆኑት እንደ ዶ/ር ደረጀ አያሌው ገለፃ በአማራ ክልል በስድስት ወረዳዎች የመኮረኒ ስንዴ፣ ባቄላ፣ ቦቆሎ፣ ዳጉሳ እና ሌሎች የተሸሻሉ የሰብል ዝርያዎችን ለአርሶ-አደሮች አድርሷል፡፡ አክለውም ለበርካታ ዓመታት ጠንካራ ስራ በመስራት የቆይታ ጊዜውን ያጠናቀቀው የተቀናጀ የዘር ዘርፍ ልማት (ISSD Ethiopia) ተሞክሮ ያላቸው አርሶ-አደሮችን በማሳተፍ  በአሳታፊ አሸናፊ የሰብል ዝርያዎችን የማስፋት ፕሮጀክት (Upscaling Crowdsourced ‘’winner’’ seed varieties project) ከላይ ከተጠቀሱት የሰብል ዝርያዎች ዉስጥ የባቄላን፤ የመኮረኒ ስንዴን እና የዳጉሳ ዘሮችን ለአርሶ-አደሮች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በማድረስ እና ለገበሬዎች የህብረት ስራ ማህበራት ስልጠናዎችን በመስጠት የወረዳ የግብርና ባለሙያዎች ጠንካራ የክትትል ስራ ተጨምሮበት በዘንድሮ የሰብል ወቅት በመስክ ምልክታ እንደታየው አመርቂ ውጤት መገኘቱን ዶ/ር ደረጀ ገልፀዋል፡፡ አርሶ-አደሮች ተጠቃሚ ከሆኑባቸው ሰብሎች መካከል  ጉሎ የመኮረኒ ስንዴ በ’’51 አርሷደሮች’’ በዶሻ የባቄላ ዝርያ በ’’107 አርሶ-አደሮች’’ በጃቪ የዳጉሳ ዝርያ በ’’54 አርሶ-አደሮች’’ በሜጫ የዳጉሳ ዝርያ በ’’52 አርሶ-አደሮች’’ እና ነጮ የዳጉሳ ዝርያ በ’’56 አርሶ-አደሮች’’ በአጠቃላይ በስድስቱም ወረዳዎች ላይ 320 አርሶ-አደሮች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በዚህ ዓመት ተሳታፉ ነበሩ፡፡

በደቡብ ጎንደር ዞነ ፋርጣ ወረዳ የሀውዘት ቀበሌ አርሶ-አደር የሆኑት አቶ አግማሴ ጌጡ እና አቶ የኔዓለም ፀዳሉ በዶሻ የባቄላ እና የመኮረኒ ስንዴ ምርጥ ዘር ተጠቃሚ አርሶ-አደሮች እንዳሉት ከፕሮጀክቱ የተሰጣቸውን ዘር ባገኙት ስልጠና እና በግብርና ባለሙያዎች በመታገዝ የዘሩት የስንዴ እና የባቄላ ሰብል ከጠበቁት በላይ ምርት እንደሚሰጣቸው ተናግረው ፕሮጀክቱ ቀጣይ የተሻሻሉ ምርጥ ዘር በማቅረብ በርካታ ገበሬዎችን የእድሉ ተጠቃሚ በማድረግ አሁን ላይ ያለውን የምርጥ ዘር እጥረት ለመቀነስ የበኩሉን አስተዋፅፆ እንዲያበረክት ጠይቀዋል፡፡ በተመሳሳይም የምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረኤሊያስ ወረዳ የጥጃ ጎጠር ቀበሌ የላቀ ማርቆስ የገበሬ ህብረት ስራ ማህበር አርሶ-አደሮች ፕሮጀክቱ ምርጥ ዘር በማቅረብ እና የተለያዩ ሙያዊ ስልጠናዎችን በመስጠት አርሶ-አደሩ በምግብ እህል እራሱን እንዲችል በሚያደርገው የስራ እንቅስቃሴ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው የተሻሻሉ ተጨማሪ የነጮ ዳጉሳ እና የስንዴ ዝርያዎች እንዲቀርብላቸው አቶ አግማሴ ጌጡ ተናግረዋል፡፡

አሸናፊ አሳታፊ የሰብል ዝርያዎችን የማስፋት ፕሮጀክትን (Upscaling Crowdsourced ‘’winner’’ seed varieties project) ወክለው በመስክ ምልከታው ላይ የተሳተፉት ዶ/ር ሀይሉ ተፈራ ካሁን በፊት ይታዩ የነበሩ የዘር እጥረትን እና ብክነትን በመቅረፍ እና በአንድ ጊዜ በርካታ አርሶ-አደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ የተሰራውን ስራ አድንቀዋል፡፡ ይህ በእርግጥም የአሸናፊዎችን ዝርያዎች የበለጠ ለማስፋት እና የፕሮጀክት ግቦችን ለማሳካት፣ በዘር እራስን መቻል በቅርብ ጊዜ ለማረጋገጥ እና ለኢንዱስትሪዎች እና ለህብረተሰቡ ከፍተኛ የምርት ደረጃ ውስጥ ለመግባት ጥሩ አጋጣሚ ይፈጥራል ሲሉ ተናግረዋል። ዶ/ር ሃይሉ አክለውም ይህ ለተመራማሪዎች፣ የፕሮጀክት ስራ አስኪሃጆች እና የኤክስቴንሽን ባለሙያዎች አርሶ-አደሮቻች የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ ዋስትና እንዲያገኙ ቁርጠኝነትን በተላበሰ መንፈስ ከበፊቱ የበለጠ ጠንክረው እንዲሰሩ እስካሁን ለሰሩት ስራ እውቅና መስጠት ተገቢ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሰራተኞቹ ጠንክረው መሥራታቸውን እንደሚቀጥሉ እና የታለሙትን ዓላማዎች እንደሚያሳኩ ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል።  

 

 

 

5ኛው ዙር ብሔራዊ የበጎ ፍቃድ ማህበረሰብ ልማት አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነ ስርዓት በስራ ዓመራር አካዳሚ አዳራሽ ተካሄደ ፡፡

ጥቅምት 27/2015ዓ/ም (ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ) በሰላም ሚኒስቴር እና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትብብር ‹‹በጎነት ለአብሮነት›› በሚል መሪ ሃሳብ ከሁሉም ክልሎች ለተወጣጡ ከ2000 በላይ ወጣቶች ለ33 ቀናት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠው ብሔራዊ የበጎ ፍቃድ ስልጠና ማስጀመሪያ ስነ ስርዓት በስራ ዓመራር አካዳሚ አዳራሽ ተካሂዷል ፡፡   

በመርሃ ግብሩ የእንኳን መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ አብሮነት ለተለየ አላማ እና ለአዲስ ነገር ውል የምንይዝበት፣ የምንገናኘበት እንጂ የማንለያይበት፣ በጋራ ሆነን ለህዝባችን ለራሳችንና ለአገራችን የምንዘምት መሆኑን በማውሳት እንኳን ወደ ውቢቱ ባሕር ዳር በሰላም መጣችሁ ብለዋል፡፡  ‹‹በጎነት ለአብሮነት›› የሚለው ቃል ከበጎ ፈቃድ ጋር የተገናኘ በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ግምት የሚሰጠው፣ የስርዓተ ትምህርቱ አካል የሆነ አለምአቀፋዊና ኢትዮጵያዊም ነው ብለዋል፡፡

ዶ/ር ፍሬው በቆይታችሁ ለመጣችሁበት ዓላማ ( ስልጠናውን፣ መተዋወቁን፣ መረዳዳቱን፣ አብሮነት ምን ያህል እንደሚጠቅም ማወቅንና የዚህ አምባሳደር ሆኖ በህይወትም ኖሮ መስበክን ) ቅድሚያ በመስጠት እንዲሰሩ ለሰልጣኞች መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የባሕር ዳር ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ድረስ ሳሕሉ ባሕር ዳር ከተማ ፍጹም ሰላማዊ፣ የብሔርም ሆነ የሀይማኖት ግጭት የማይስተዋልባት ከተማ ናት፡፡ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በትምህርት ሚንስቴር የሰላም ዩኒቨርሲቲ ተብሎ እውቅና የተሰጠው አንድም ቀን ለብጥብጥ ተቀባይም ሰጭም ያልሆነው ሰላም ወዳድ በሆነ ማህበረሰብ ውስጥ በመገኘቱ ነው ብለዋል፡፡

የሰላም ሚንስቴር የክብር ሚኒስትሩ አማካሪ አምባሳደር እሸቱ ደሴ በጎነት ለአብሮነት በሚል መሪ ሀሳብ በሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው የተጀመረው የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር ኢትዮጵያዊ እሴቶችን፣ መርሆዎችን ለወጣቱ ትውልድ በማስተላለፍ በዘር፣ በጎሳ በሀይማኖት እና በሌሎች ማንነቶች ላይ መሰረት አድርጎ ያለውን መከፋፈል ለማስወገድ ሚናው የጎላ ስለሆነ ለአገራችን በጅጉ አስፈላጊ ፕሮግራም ነው ብለዋል፡፡

አምስተኛው ዙር ለየት የሚያደርገው አገራችን ዘርፈ ብዙ ዋጋ ያስከፈላት እና በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ተከስቶ የነበረውን ጦርነት በሰላማዊ መንገድ የተደረገው ድርድር ኢትዮጵያ በምትፈልገው መልኩ ስምምነት ላይ በተደረሰበት እና እንደ አገር ኢትዮጵያውያን ባሸነፍንበት፣ ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ የሚለውን መርህ መተግባር ባሳየንበት፣ የኃያላን እጅ ጥምዘዛ በማምከን የጥቁሮችን ዳግማዊ ድል ባበሰርንበት መሆኑ ለየት ያደርገዋል፡፡ በዚህም አምስተኛው ዙር 10ሺ ሰልጣኞች ከመላው አገሪቱ ለበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተመዘገቡ ሲሆን በተመሳሳይ ጊዜ በአምስት ዩኒቨርሲቲዎች ማለትም በባሕር ዳር፣ በጅማ፣ በደብረ ማርቆስ፣ በዋቻሞ እና በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲዎች ስልጠናው የሚሰጥ ይሆናል ብለዋል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃኑ ገድፍ የሰላም አምባሳደር ለሚሆኑ ወጣቶች በዩኒቨርሲቲው ቆይታቸው ምን ማድረግ እንደሚኖርባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አስተባባሪ አቶ ዘውዴ ኤጄርማ በበኩላቸው ሰልጣኞች ለ33 ቀናት የሚቆዩ ሲሆን ወጣቱ አገሩን የሚወድ፣ ስነ መግባር ያለው፣ የስራ ባህል ያለው፣ ምክኒያታዊ የሆነ ወጣት እንዲፈጠር እና ለህብረተሰቡ የሚያገለግል ሆኖ እንዲወጣ ይደረጋል ብለዋል፡፡

በአማራ ክልል ፖሊስ ባንድ በደመቀው መርሃ ግብር የሰላም ሚኒስቴር አመራሮች፣ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አመራሮችና ሰራተኞች እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች ታድመውበታል፡፡

 

 

 

 

  

 

 

 

ለአብያተ መጽሀፍት ዳይሬክቶሬት ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ዳይሬክቶሬት ከዩኒቨርሲቲው አብያተ መጽሀፍት ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር ከጥቅምት 21 እስከ 24/2015 ዓ/ም ድረስ በሁለት ተከታታይ ዙር ለአብያተ መጽሀፍት ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አብያተ መጽሀፍት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እሱባለው ሰንደቄ የስልጠናውን አስፈላጊነት ሲናገሩ በመጽሀፍት ውሰት ጊዜ ስራን ለማቀላጠፍ፣ መረጃዎችን ለማጠናከር ብሎም የሚዛባውን መረጃ ለማስተካከል ይጠቅማል ብለዋል፡፡

አቶ እሱባለው አክለውም ስልጠናው ካሁን በፊትም በሶስቱ የአብያተ መጽሀፍት ያሰራር ዘዴዎች አውቶሜሽን ስርዓት፣ ዲጅታል ቤተ-መጽሀፍት፣ ተቋማዊ ሪኩዚት ዙሪያ ለእያንዳንዱ ሰራተኛ ሙያዊ ስልጠና በመሰጠቱ ስራው ከ90% በላይ በሲስተም እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

ስልጠናውን ሲሰጡ ያገኘናቸው በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አይ ሲ ቲ ዳይሬክቶሬት ስር የመማር ማስተማር ቡድን መሪ አቶ ፈንታሁን መኩሪያው በበኩላቸው ይህ ስልጠና የተዘጋጀው በላይብረሪ ውስጥ ካሉት የስራ ክፍሎች መጽሀፍት ለሚያውሱ ባለሙያዎች መጽሀፍትን ለተጠቃሚዎች ማዋስ የሚያስችላቸውን ሲስተም ሲሆን ነገር ግን መብራት በሚጠፋበት ስዓት ተጠቃሚዎች እንዳይጉላሉ እራሳቸው ኮምፒዩተር ላይ መረጃ እያስቀመጡ ኢንተርኔት ሲመጣ መረጃ ኮፒ እያደርጉ መጠቀም የሚያስችል ስልጠና ነው ብለዋል፡፡

አቶ ፈንታሁን መጽሀፍ በሚያውሱበት ጊዜ ከአሁን በፊት በተደጋጋሚ የሚጠይቋቸውን ከአስር በላይችግሮችን ዘርዝረን በማውጣት እነዚህ ችግሮች ሲያጋጥሟቸው ወደ እኛ ሳይመጡ እራሳቸው እንዴት መፍታት እንደሚችሉ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ተችሏል፡፡ አጠቃላይ በዩኒቨርሲቲው አይ ሲ ቲ ዘርፍ በርካታ የሲስተም ስራዎች የተሰሩ ሲሆን በአብያተ መጽሀፍት ክፍልም ሶስት ሲስተሞች ሰርተን አስረክበናል ብለዋል፡፡   

በስልጠናው ማጠቃለያ ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ዳይሬክተር አቶ ወርቁ አበበ ስልጠናው ያስፈለገበትን ምክንያት ሲገልፁ ባለሙያው ከዘመኑ ቴክኖሎጅ ጋር እንዲተዋወቅ እና በሙያው ያለውን ክፍተት ለመሙላት እንደሚያስችለው ተናግረዋል፡፡ ከስልጠናው በኋላም አገልግሎቱ እንዴት እየተሰጠ ነው፣ ምን ያህል ውጤታማ ሁነዋል በሚል ጥናት አድርገን አሁንም ክፍተት ከተገኘ ተጨማሪ ስልጠና እንደሚሰጥ ገልፀዋል፡፡

 

የባሕር ዳር ከተማን መዋቅራዊ ፕላን ከተማ አስተዳደሩ ተረከበ

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር የባሕር ዳር ከተማን የሚያዘምን መዋቅራዊ ፕላን ሰርቶ ለከተማ አስተዳደሩ አስረክቧል፡፡

 

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ በርክክብ ስነስርዓቱ  እንደገለጹት የባሕር ዳር ከተማን መዋቅራዊ ፕላን በዘመናዊ መልኩ ለመስራት ዩኒቨርሲቲው ጽ/ቤት አቋቁሞ የተለያየ ሙያ ያላቸውን ሙያተኞች በማሳተፍ ለሌሎች ከተሞች ተሞክሮ የሚሆን ፕላን በመስራት ማስረከብ መቻሉ አኩሪ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል፡፡

 

ፕሬዘዳንቱ አክለውም ፕላኑን ለመስራት ከአንድ መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ይፈጅ የነበረውን በ20 ሚሊዮን ብር በማህበረሰብ አገልግሎት ስም ሰርቶ ማስረከቡ ይበል የሚያስብል ተግባር መሆኑን ገልፀው ባሕር ዳር ከተማ የክልል ዋና መዲና እንደመሆኗ መጠን ውብና ማራኪ ብትሆንም  በተለየ መልኩ ደምቃ የምትታይ ከተማ ለማድረግ ፕላኑ መዘጋጀቱን አንስተዋል፡፡ ከተማ አስተዳደሩም  መሪነቱን በመውሰድ በምናብ ውብ ሆና የምትታየውን ከተማ እውን ለማድረግ በቅንጅትና በፍጥነት  ሁሉን  ባሳተፈ ርብርብ ወደ ትግበራው መግባት ቀዳሚው ተግባር መሆኑን በአንክሮ ተናግረዋል፡፡

 

የባሕር ዳር ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ ክቡር ዶ/ር ድረስ ሳህሉ አንድ ከተማ ተውባና ማራኪ ሆና እንድትታይ ከሚያደርጓት ነገሮች አንዱና ዋናው ደረጃውን የጠበቀ መዋቅራዊ ፕላን ስለሆነና ይህን ስራ በኃላፊነት ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ወስዶ መስራቱ እጅግ በጣም  የሚያስመሰግን መሆኑን ተናግረዋል፡፡

 

ዶ/ር ድረስ በማስከተል ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲና ባሕር ዳር ከተማ የማይነጣጠሉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች መሆናቸውን አውስተው ዩኒቨርሲቲው የምሁራን መንደር በመሆኑ ይህንን መዋቅራዊ ፕላን  ጊዜ በመውሰድ በርካታ ሙያተኞችን፣የአገር ሽማግሌዎችንና የሚመለከታቸውን የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በተደጋጋሚ መድረክ ምክረ-ሃሳብ በመቀበል መስራቱ አኩሪ ተግባር መሆኑን በአንክሮ ገልፀዋል፡፡

 

በመርሃ ግብሩ ላይ መዋቅራዊ ፕላኑን በተመለከተ የኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ከባሕር ዳር ከተማ መዋቅራዊ ፕላን ፕሮጀክት ጽ/ቤት ጋር በጋራ ያዘጋጁት ተንቀሳቃሽ ምስል ለታዳሚዎች ቀርቧል፣ በፕሮጀክቱ አባላት የተለያዩ ይዘት ያላቸው የፅሁፍና የምስል ገለፃ ቀርቧል፣ በቀረቡት ፅሁፎች ዙሪያ በዶ/ር ፍሬው፣በዶ/ር ድረስ እና የፕሮጀክቱ ዳይሬክተር በሆኑት ዶ/ር መንግስቴ አባተ መሪነት ውይይቱ ተካሂዶ ታዳሚዎች የተሰራው ፕላን እንደ አስደሰታቸውና በቅርብ ወደ ትግበራው መግባት ተገቢ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

It is our pleasure to have felt our presence in the community through our continually growing community services. We will continue putting our finger prints in the future in a more pronounced manner.

We would like to warmly accept the commendment.

Bahir Dar University

Pages