Latest News

የዩኒቨርሲቲያችን ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ ከ”Ebs አዲስ ነገር” ጋር ቆይታ አድርገዋል::
በቆይታቸው ስለ ዩኒቨርሲቲያችን፡-
ለሃገር ሁለንተናዊ ዕድገት ምሁራንን ከማፍራት ጀምሮ ስላለው አበርክቶ፣ የትምህርት ፕሮግራሞች ብዛት፣ ለባሕር ዳር ከተማ ያለው ፋይዳ፣ ስለተቋማዊ ነፃነት፣ 60ኛ አመት አከባበር አስመልክቶ፣እና ስለሌሎች ዋናዋና ጉዳዮች ማብራሪያ ሰጥተዋል፤ ሊንኩን በመጫን እንዲከታተሉ ጋብዘናል፡- https://youtu.be/EJ0FQN_0mtI

Prof. Teketel Yohannes is currently Chief Executive Director of Ethiopian Academy of Sciences (EAS). He was among the founding staff of Chemistry Department at the former Bahir Dar Teachers College (Peda). In this video, he narrates why Peda and Poly merged to grow to BDU than Blue Nile University. He also discusses the special effort of Dr. Demissie Manahilot in shaping young instructors behavior and developing the college. In his speech, he emphasized the meaningful and intimate relationship that existed between administrative and academic staff in his 16 years of service at Peda.

He generally described how much Bahir Dar Teachers College and Bahir Dar city have impacted his life, from his family (forming spouse relationships and having four children) to his professional life (earning his Masters and Doctoral degrees).

This made him always feel like returning back to home whenever attending academic and research deliverables at the university. He was also grateful for all these and recognized the good times he had with the college community.

Lastly, he called all those who worked in Peda to come and celebrate BDU'S and Peda's Diamond and Gold Jubilee celebrations respectively.

Click here to listen the professor's talk: https://www.youtube.com/watch?v=Hgtz6KWl8qE

Public Lecture on two crucial topics

By Dr. Yonas Gizaw and Mr. Eyob Easwaran

The detail is available on the poster attached.

Brief bio of the presenters

 

Dr. Yonas Gizaw is Principal Scientist, at the Procter and Gamble Co (P&G) and Adjunct Professor of Carbohydrate Chemistry at Purdue University. Prior to joining P&G he had PhD in chemistry from Purdue University. His current responsibilities include leading technology for advanced cleaning technologies, surfaces and interface sciences, nanotechnology.  Prior to his current assignment, Dr. Yonas held technical leadership positions in strategic and innovation technologies for detergent and cleaning products, food and beverages. His innovative and patented technologies have generated hundreds of millions of USD revenue for the company. 

 

Dr. Yonas has received numerous awards and recognitions for his innovation and leadership. Among them are Distinguished Purdue Agriculture Alumni Award, Outstanding Food Science Award (Purdue) Innovation Award, (P&G), Connect and Develop Award (P&G), Mastery & Excellence Award (P&G),  Excellence in Chemistry Award (Alabama A&M), Lloyd Ferguson Young Scientist Award (NOBCChE), Community service Award, (African Professional Network- USA) and had led AACC –International Chairman of Carbohydrate Division, Institute of Food Technologists, the Carbohydrate Division, the Global Sustainability Special Interest Teams in P&G etc.. He has served as advisory board for International Life Science Institute, The Whistler Center for Carbohydrate Research, Purdue University, University of Cincinnati Sub-Saharan group, APNET, and is the co-founder of Alliance for Research, Innovation and Education (AfRIE). 

 

Mr. Eyob Easwaran is a seasoned Project Finance and Private Equity professional with over 30 years of experience in the power and finance industries in various capacities including equity and debt investing, engineering, project financing, construction, and asset and risk management for private equity funds and other financial institutions.  Since December 2017, Mr. Eyob is serving as Lender Transaction Advisor on Power and Infrastructure for the Trade and Development Bank for Eastern and Southern Africa.  Most recently, he served as Director of Development for Black Rhino based in Addis Ababa.  Prior to that, he was a Managing Director and Director of Asset Management at Power Capital Partners LLC, a start-up private equity firm formed in partnership with Hunt Power, a wholly owned subsidiary of Hunt Consolidated, Inc., to invest in the development of fully contracted or hedged power projects.

 

Previously, Mr. Eyob Easwaran was a Partner and Lead Asset Manager at Conduit Capital Partners, a private equity firm that invested in power projects in Latin America and the Caribbean. In this capacity, Mr. Eyob Easwaran managed a portfolio of independent power projects with approximately 1,000 MW of aggregate installed capacity and a total investment of approximately $1.5 billion employing a range of conventional and renewable generation technologies in nine countries throughout Latin America and the Caribbean. Mr. Eyob Easwaran was a member of the investment committee of the fund and was involved in several acquisition and divestment transactions.

Mr. Eyob Easwaran, a native of Ethiopia, received a B.E. Degree in Mechanical Engineering from Jose Antonio Echeverria Polytechnic Institute in Havana, Cuba, a Post-Graduate Diploma in Geothermal Technology from Auckland University in New Zealand and M.Sc. Degree in Business/Finance from Johns Hopkins University.  He has also attended short-term programs on Geothermal Energy in Japan and Iceland.

 

ለ18ኛ ጊዜ የፀረ-ሙስና ቀን ተከበረ

 (ህዳር 26/2015 ዓ.ም፣ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-BDU) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ19ኛ ጊዜ በአገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ18ኛ ጊዜ የተከበረውን የፀረ-ሙስና ቀን በዩኒቨርሲቲው የመሰብሰቢያ አዳራሽ "ሙስናን መታገል በተግባር!" በሚል መሪ ቃል አከበረ፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ጉዳዮች ም/ፕሬዘዳንት አቶ ብርሃኑ ገድፍ ሁሉም ማህበረሰብ ሙስናን መፀየፍ እንደሚገባውና ከሙስና የፀዱ እጆች በየእምነታችን እንደሚያስፈልግ በአንክሮ ገልፀዋል፡፡

አቶ ብርሃኑ በማስከተል በሙስና ወንጀል የተሰማራ ሰው ሌሎች ንፁኃንን ሲያሳድድና ከተቋሙ ይልቅ የግሉን ገፅታ ለመገንባት ከፍተኛ ጥረት ስለሚያደርግ በዚያ ግርግር  ለእውነት የቆሙ ሰዎች ሳይሸማቀቁ በተገቢው ሰዓት ተገቢውን መረጃ ለሚመለከተው አካል በማሳወቅ የሙስና ወንጀልን መከላከል እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

አቶ ብርሃኑ አክለውም በሙስና ወንጀል የተሰማራ ማንኛውም ሰው በእምነቱም ሆነ በማህበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ስለሌለው የሚያከናውናቸው ተግባራት ሁሉ ውጤታማ እንደማይሆኑ በግልፅ የታወቀ ስለሆነ በንጽህና ሰርተን ተቋማችንን ማሳደግ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኢ/ር አለማየሁ ተፈራ ባቀረቡት የውይይት መነሻ ፅሁፍ "ሙስናን መታገል በተግባር!" መሆኑን የሚያመላክቱ በርካታ ሃሳቦችን ዳሰዋል፡፡

የሙስና ወንጀል ከሌሎች የተለየ የሚያደርገው በረቀቀ ስልት የሚፈፀምና የወንጀሉን ባለቤት ለማወቅ ረጅም ጉዞን የሚጠይቅ ብሎም ተዋናዮች ወንጀሉን እንደ ነውር የማይቆጥሩ በመሆኑ ለማህበረሰቡ ዋነኛ የእሮሮ ምንጭ መሆኑን ከፅሁፉ መረዳት ተችሏል፡፡

በመድረኩ ላይ ተገኝተው የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ማኔጅግ ዳይሬክተር ኮማንደር ፈንታሁን አየለ በንግግራቸው ሙስና እንዲጎለብት ከሚያደርጉት ነገሮች አንዱና ዋናው የስራ ኃላፊዎች ቁርጠኝነት መላላት ሊሆን ስለሚችል ሁሉም ተረባርቦ ሙስናን መዋጋት እንዳለበት ተናግረዋል፡፡

ኮማንደሩ አክለውም የሙስናን ወንጀል ለመከላከል የፀረ ሙስና ባለሙያ ወንጀሉን ሲያጋልጥ የተቋማት ኃላፊዎች በጥላቻ ዓይን የማየት ልምድ በማስወገድ ንፁህ ህሊና ይዘን ያለምንም እንከን ማንነታችንን ብቻ ለትውልድ ማስተላለፍ ተገቢ መሆኑን አንስተዋል፡፡

``ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ``

``Wisdom at the source of Blue Nile

Thank you for visiting and inviting our Pages!

Thank you for your likes, comments and shares!

ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

Facebook፡ https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube፡ https://www.youtube.com/@bduethiopia

Instagram፡www.instagram.com/bduethiopia

TikTok፡ https://www.tiktok.com/@bduethiopia

Telegram፡ https://t.me/bduethiopia

Twitter፡ https://twitter.com/bduethiopia

LinkedIn፡http://www.linkedin.com/school/bduethiopia

Website https://bdu.edu.et/

#BDU60th_ANNIVERSARY

 

Veteran instructors from Amharic Department, BDU_ from camera left to right: Dr. Marew Alemu, Gash Ashenafi Tesfaye, the late Dr.Tesfaye Abera, Dr. Bedilu Wakjira and Dr. Anteneh Aweke taking a moment of memorial photo shoot with their graduating student in the 90s.

5ኛው ዙር የበጎነት ለአብሮነት ብሔራዊ አገልግሎት ሰልጣኞች እንቦጭን በመንቀል ተሳተፉ

(ሕዳር 22/2015ዓ/ም ፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ)  የ5ኛው ዙር የበጎነት ለአብሮነት ብሔራዊ አገልግሎት ሰልጣኞች በባሕር ዳር ከተማ አፄ ምኒልክ ክፍለ ከተማ ሰባታሚት ቀበሌ የአባይ ወንዝ በሚያዋስናቸው አካባቢዎች የእንቦጭ አረምን በመንቀል በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራዎች ላይ ተሳተፉ፡፡

ሰልጣኞችን ሲያስተባብሩ ያገኘናቸው ረዳት አሰልጣኝ ኢምራን አብዱሰመድ እንዳሉት በእንቦጭ ማረም ስራው ሁሉም የ5ኛው ዙር የበጎነት ለአብሮነት ብሔራዊ አገልግሎት ሰልጣኞች የተሳተፉ ሲሆን ካሁን በፊትም ከምግባቸው ቀንሰው ለጎዳና ተዳዳሪዎች ምግብን ማጋራታቸዉን ተናግረዋል፡፡

በአፄ ምኒልክ ክፍለ ከተማ ሰባታሚት ቀበሌ አስተዳደር የሰብል፣ አትክልትና ፍራፍሬ ባለሙያ አቶ ገበያው አስቻለው አባይ ወንዝ በሚያዋስናቸው ምዕራብና ምስራቅ አቅጣጫ ለመስኖ ስራ እንዲውል በተሰሩ ቦዮች ሁሉ በእንቦጭ አረም ተወረዉ የሚገኙ ሲሆን ይህን ለመከላከል እንደ ክልል በሚሰራው የተፈጥሮ ሀብት ስራ አርሶ አደሮችን እና የአካባቢውን ህብረተሰብ በማስተባበር እየሰራን እንገኛለን ብለዋል፡፡ ዛሬ ላይ በ5ኛው ዙር የበጎነት ለአብሮነት ብሔራዊ አገልግሎት ስልጠና የወስዱ ወጣቶች በቀበሌያችን ተገኝተው የእንቦጭን አረም ለማስወገድ ያደረጉት አስተዋፅዖ ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡

በበጎ ፈቃድ የተሰማራችው ተማሪ ብርቱካን ወንዴ በበኩሏ ከአሁን በፊት ብዙ የበጎ ስራዎች ላይ መሳተፏን ገልፃ አሁን ላይ በብዙ ቦታዎች ተንሰራፍቶ የሚገኘውን እንቦጭ በመንቀል የዜግነት ግዴታዋን በመወጣቷ ደስተኛ መሆኗን ተናግራለች፡፡

 

Damtew Darza (PhD) who has been president of Arbaminch University for the last 6 years graduated together with his elder brother Digafe Darza (PhD) in 1982 E.C from the former Bahir Dar Teachers College in Pedagogical Sciences program. Dr. Damtew got his PhD in Educational Psychology whereas Dr. Digafe earned PhD in Educational Leadership and Policy Studies. Like his younger brother, Dr. Digafe is serving at Arbaminch University.

የዶ/ር አበባ ብርሐኔን ሕዝበ-ገለፃ ይታደሙ። እንዳያመልጥዎ!

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፍሬ ስለሆነችውና በስራዎቿ  ዓለም-አቀፍ ታዋቂነትን ስላገኘችው ዶ/ር አበባ BBC News አማርኛ በሰኔ 2014ዓ.ም የሚከተለውን አስነብቦ ነበር።

****

80 ሚሊዮን ምሥሎችን ያሰረዘችው ኢትዮጵያዊቷ ኮግኒቲቭ ሳይንቲስት ዶ/ር አበባ ብርሃኔ

 

የክፍሏ ጎበዝ ተማሪ ነበረች።

 

ሰኔ ላይ ሰርተፍኬት ለመቀበል ቀድመው ከሚሰለፉ መካከል ናት።

 

ዛሬ በዓለም ገናና ስም ካላቸው ኮምፒውተር ሳይንቲስቶች አንዷ የሆነችው አበባ ብርሃኔ (ዶ/ር)፣ ያኔ ሰርተፍኬት የምትወስደው አባቷ እሽኮኮ ብለዋት ነበር።

 

ውጤቷ ሁሌም ያኮራቸዋል። በየትምህርት ዘመኑ መጨረሻ እሽኮኮ ብለዋት አብረዋት ሰርተፍኬት ይቀበላሉ። ከዚያ ደስታ ከረሜላ ይገዛላታል።

". . . ደስታ ከረሜላ ገዝቶልኝ ጠጅ ቤት ይወስደኝ ነበር። ከዚያ ለጓደኞቹ በኩራት ያሳየኛል። ይህ ደስ የሚለኝ ትውስታዬ ነው። ዛሬ የደረስኩበት ለመድረሴ አባቴ ትልቅ ሚና አለው። ፀጉሬን ሁሉ የሚሠራኝ እሱ ነበር. . ."

 

አባቷ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ዘጠኝ ዓመቷ ላይ ነው። በሕይወት ሳሉ ለትምህርት ፍቅር እንድታሳድር አበረታተዋታል።

 

ነዋሪነቷን በአየርላንድ፣ ደብሊን ያደረገችው አበባ፣ በቅርቡ መነጋገሪያ ያደረጋት የማሳቹሴትስ ኢንስቲቲዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ (ኤምአይቲ) 80 ሚሊዮን ምሥሎችን እንዲያጠፋ ያደረገውና የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃንን ዘገባ የተቆጣጠረው ጥናቷ ነው።

 

ለቤተሰቧ ብቸኛ ሴት ልጅ ናት።

 

እናቷ "ሴት ልጅ ወደ ማጀት" ይሏት ነበር። የሴትን መማር እምብዛም በማይደግፍ ቤተሰብ ውስጥ ማደግ ለትምህርት ትኩረት መስጠትን ከባድ ቢያደርገውም ትምህርት ትወድ እንደነበር ትናገራለች።

 

እዚህ ጋር መምህሮቿን ሳታመሰግን አታልፍም።

በተለይ የዘጠነኛ ክፍል ፊዚክስ አስተማሪዋን።

ለሳምንታት ትምህርት ለማቋረጥ ስትገደድ ወደ ትምህርት ቤት የመለሷት እሳቸው ናቸው። ከዚያ በኋላም በተደጋጋሚ ትምህርት አቋርጣ ተመልሳለች።

 

መንገዱ ቀላል ባይሆንም ለትምህርት ያላት ፍቅር እንዳበረታት ትናገራለች።

 

ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ስትገባ ፊዚክስ አጠናች። ስትመረቅ አየርላንድ ነጻ የትምህርት ዕድል አገኘች።

ዓለም አሉኝ ከምትላቸው የኢትዮጵያ የዘር ሐረግ ያላቸው ኮምፒውተር ሳይንቲስቶች መካከል አንዷ ናት። ትምኒት ገብሩ፣ ረድኤት አበበ እና አበባ ብርሃኔ።

 

አበባ የኮግኒቲቭ ሳይንስ ምሁር ናት። የቋንቋ፣ የሥነ ልቦና፣ የፍልስፍና፣ የኮምፒውተር ሳይንስ፣ የአንትሮፖሎጂ (ሥነ ሰብ) እና የአርቴፍሻል ኢንተለጀንስ (ሰው ሠራሽ ልኅቀት) ጥምር ጥናት ነው።

 

የክፍሏ ጎበዝ ተማሪ ሳለች ጠጅ ቤት እሽኮኮ ተብላ የምትወሰደው ዶ/ር አበባ ዛሬም የትምህርት ሰው ናት።

 

". . . ብዙ ሕይወቴን በትምህርት ውስጥ ነኝ። አሁን የምሠራው በጣም የምወደውን ነገር ነው። ፍትሕ ማስፈን፣ ጥሩ መስሎ ከውስጡ ግን ችግር ያለውን ነገር ማጋለጥ ነው በፍቅር እንድሠራ የሚገፋኝ. . ."

 

በኮግኒቲቭ ሳይንስ እና አርቴፍሻል ኢንተለጀንስ [ኤአይ] አማካይ ላይ ታተኩራለች። ሥራዋ አእምሮን፣ አካባቢን፣ ማኅበረሰብን፣ ባህልን፣ ታሪክን መረዳት፣ ከዚያም ፈትሾ መተቸትን ያካትታል።

 

ከኤአይ ቅጥያዎች አንዱ ማሽን ለርኒንግ ሲሆን፣ ሰው ሠራሽ ማሽን መረጃ (ዳታ) ተመግቦ በተሻለ ቅልጥፍናና ትክክለኛነት ክንውን እንዲፈጽም የሚያስችል ዘመነኛ ቴክኖሎጂ ነው።

 

አበባ ለማሽን የሚቀርበውን መረጃ ትመረምራለች። ከሥነ ምግባር አንጻርም ትተቻለች። የዶክትሬት መመረቂያ ጽሑፏን እንደ ማሳያ እንውሰድ።

ትክክለኛ ነው ብለን መገመት የለብንም።"

ነገሩን ወደ ኢትዮጵያ አውድ እንውሰደው።

 

ሰልፊ መለጠፍ እናቁም?

 

አበባ በኢትዮጵያ በዋነኛነት የሚያሰጋት የግል መረጃ አጠባበቅ ግንዛቤ አለመኖሩ ነው።

". . . ምሳሌ ልስጥሽ፣ የማትሪክ ውጤት ሲወጣ ሰው ውጤቱን፣ መታወቂያ ቁጥሩንና ሌላም የግል መረጃውን በዘፈቀደ በበይነ መረብ እየለጠፈ ነበር። ይህ የግል መረጃ ሲለቀቅ ግዙፍ የቴክኖሎጂ ተቋሞች ሀርቨስት (ይሰበስቡታል) ያደርጉታል። ከዚያም ሰዎችን ለማግለልና ለመጉዳት ይውላል። በበይነ መረብ የምንለቀው መረጃ አንዴ ከተለቀቀ በኋላ እንደማይጠፋና እየተንሳፈፈ እንደሚቆይ ማወቅ አለብን. . ."

ሌላው ጥንቃቄ ልንወስድበት የሚገባው ነገር የራስን ምሥል (ሰልፊ) በዘፈቀደ መለጠፍ ነው።

ብዙ ኢትዮጵያዊ ምን ችግር አለው? ብሎ ሰልፊ እንዳሻው ይለጥፋል። ሆኖም ምሥሉ ወደ መረጃ ቋት (ዳታቤዝ) እንደሚገባ፣ ከዚያም ማሽን ለማሠልጠን እንደሚውል መታወቅ አለበት።

አሁን ላይ ለታክሲ፣ ለባንክ ወይም ምግብ ለማዘዝም መተግበሪያ እየተጠቀምን እንገኛለን።

የግል መረጃችንን በስፋት በበይነ መረብ ስንለቅ ይህ መረጃ ይከማችና ኋላ ላይ አገልግሎት ስናገኝ የመድልዎ ሰለባ እንድንሆን ይጋብዛል።

"ወደድንም ጠላንም የሰዎችን ታሪክ፣ የገንዘብ ልውውጥ፣ ብሔር እና ሌላም የግል መረጃ በመጠቀም ብድር እንስጣቸው ወይስ አንስጣቸው? የሚለው እየተወሰነ ያለበት ዓለም ነው። ኢትዮጵያውያንም ወደዚያው መንገድ እየሄድን ነው።"

 

ብዙ ጥቁር ሴቶች በሙያው አይታዩም።

". . . ወደ 1950ዎቹ ስንሄድ ከኮምፒውተር በፊት የሒሳብ ስሌት የሚሠሩት ጥቁር ሴቶች ናቸው። ሙያው በጣም እያደገ ሲመጣ ግን ነጭ ወንዶች ወደ ላይ ወጡ። ከዚያ ለጥቁር ሴቶች ለመግባት ፈታኝ አደረጉት። ደስ የሚለው ግን አሁን ባለንበት ዘመን በጣም ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረጉ ያሉት የሐበሻ ሴቶች መሆናቸው ነው።"

 

አበባ ይህንን የምትለው ያለ ምክንያት አይደለም። በሙያዋ ከምትኮራባቸው ቅጽበቶች አንዱ እሷ ትምኒት ገብሩ እና ረድኤት አበበ የተገናኙበትን መድረክ ነው።

 

አምና ኒውፒርስ በተባለ የውይይት መድረክ ላይ ሦስቱም ንግግር እንዲያደርጉ ተጋብዘዋል።

"ጥሩ የትብብር መስመር ዘርግተናል። እንረዳዳለን፣ አብረን እንሠራለን። አለበለዚያማ ዘርፉ ለጥቁር ሴት ፈታኝ ነው። ፒኤችዲ ለመሥራት ከነጭ ወንድ በላይ ያንቺ ፈተና ይበዛል። ይህን ሁሉ አልፈን እዚህ መድረሳችን ያኮራል።"

ዓለም አሉኝ ከምትላቸው ባለሙያዎች አንዷ የሆነችው ዶ/ር አበባ

አምና በኤአይ እጅግ ተጽዕኖ ፈጣሪ ከሆኑ አንዷ ተብላ ተመርጣለች።

 

በኮምፒውተር ቪዥን ፈጠራ ቬንቸር የተባለው ሽልማት ተሰጥቷታል።

በሆል ኦፍ ፌም፣ በ100 ብሩህ የኤአይ ባለሙያ ሴቶች ዝርዝር ውስጥ ገብታለች።

በኤአይ ዘርፍ በአፍሪካ ተጽዕኖ ፈጣሪ ከሆኑ 80 ባለሙያዎች አንዷ ናት።

ከሽልማቶቿ ዋና ዋናውን ጠቀስን እንጂ ያገኘቻቸው ዕውቅናዎች እነዚህ ብቻ አይደሉም።

ለእሷ ግን ትልቅ ዋጋ ያለው ቅጽበት የፒኤችዲ መመረቂያ ጽሑፏን አቅርባ ያጠናቀቀችበት ነው።

". . . ገና ትልልቅ ሕልሞች አሉኝ። ግን ፒኤችዲዬን ዲፌንድ አድርጌ ከቫይቫ ስወጣ የነበረውን ቅጽበት አልረሳውም። ከ5 ዓመታት ሥራ በኋላ የደረስኩበት ስለሆነ ትልቁ ከፍታዬ ነው።"

ጽሑፏን አቅርባ ስትወጣ የተነሳው ፎቶ ትዊተር ላይ ከተለቀቀ በኋላ የእንኳን ደስ አለሽ መልዕክት ጎርፎላታል።

 

Manu, [27/11/2022 01:14]

የሙያ አጋሮቿ ትምኒት እና ረድኤት ያሉበት ብላክ ኢን ኤአይ ተቋም፣ ጥቁር ሴቶች በዘርፉ እንዲተሳሰሩ፣ እንዲተባበሩ መንገድ ከፍቷል።

ከጥናቶቻቸው አንዱ በአፍሪካውያን የኤአይ ባለሙያዎች የሚሠሩ ምርምሮች እንዴት ተደራሽ ይሁኑ? የሚለው ነው።

 

ስለ ሕብረተሰብ ጤና እና ስለ መድኃኒት የሚሠሩ የአፍሪካውያን ጥናቶች ሳይታተሙ ይቀራሉ። ሲታተሙም ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዕውቅና አይሰጣቸውም።

 

አበባ ቀጣይ ዕቅዷ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እየተቋቋመ ያለውን የኮግኒቲቭ ሳይንስ ክፍል

 መደገፍ እንደሆነ ትናገራለች። አንድ ሁለቴም በዩኒቨርስቲው ግብዣ ሌክቸር ሰጥታለች።

". . . አሁን ጥናቴ በሌሎች አገሮች ተሞክሮ ላይ የተመረኮዘ ቢሆንም፣ ዞሬ ዞሬ ግቤ ወደ ማኅበረሰቤ ተመልሼ ለእኛ መሠረታዊ የሆኑ ነገሮችን መፈተሽና አስተዋጽኦ ማበርከት ነው. . ."

ሰልጣኞች ለችግረኛ ህፃናት እና አቅመ ደካሞች የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም አካሄዱ

*********************************************************************

(ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ህዳር 14/3/2015 ዓ.ም) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከሰላም ሚኒስትር ጋር በመተባበር "በጎነት ለአብሮነት" በሚል መሪ ቃል ከሁሉም ክልሎች ተውጣጥተው በብሔራዊ በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዙሪያ ስልጠና እየወሰዱ ያሉ ከ1,200 በላይ የዩኒቨርሲቲ ምሩቃን ወጣቶች የቁርስ ወጭአቸውን በባሕር ዳር ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች በጎዳና ላይ ለሚገኙ ሕፃናት እና አቅመ ደካሞች እንዲውል በማድረግ የምገባ ፕሮግራም እና የአቅመ ደካሞችን ልብስ በማጠብ ከበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስልጠናቸው ጎን ለጎን ህብረተሰቡን የሚጠቅም በጎ ተግባር እየሰሩ መሆኑ ተገለፀ፡፡   

የአምስተኛ ዙር የብሔራዊ በጎ ፈቃድ አግልግሎት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ዘውዴ ኤጄርሳ እንደገለጹት ለአምስተኛ ዙር በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እየሰለጠኑ ያሉ 1,200 በላይ ወጣቶች ሀገራቸውን እና ሕዝባቸውን የሚወዱ የዩኒቨርሲቲ ሙሩቃን መሆናቸውን ተከትሎ በጎነትን በማህብረሰቡ ውስጥ ገብቶ የማስተማር  ተግባር  ለመፈፀም ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ከሚወስዱት ስልጠና ጎን ለጎን የቁርስ ወጫቸውን ጎዳና ላይ የወደቁ እና በልቶ ማደር ላልቻሉ ወገኖች የምገባ ፕሮግራም ከማድረጋቸው በተጨማሪ የአረጋዊያንን ልብስ በማጠብ፣ ደም የመለገስ እና የልብስ ማሰባሰብ በጎ ስራዎችን በህብረተሰቡ ውስጥ በመግባት እየሰሩ መሆኑን አቶ ዘውዴ  ተናግረዋል፡፡  

ስልጠናው የሚመራው በሰላም ሚኒስቴር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር እየተሰጠ መሆኑን የተናገሩት አስተባባሪው የስልጠናው ዋና ዓላማ በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የሙያ መስኮች ተመርቀው ያለስራ የተቀመጡ ወጣቶች የበጎ ፈቃድ ስራን ለመስራት መስፈርት ወጥቶላቸው ምዝገባ አካሂደው ስልጠናውን በአምስት ዩኒቨርሲቲዎች እየወሰዱ መሆኑን አስተባባሪው ተናግረዋል፡፡ አክለውም በተለያየ ጊዜ በሀገራችን ከውስጥም ሆነ ከውጭ የህብረተሰባችን ሰላም ለማደናቀፍ ጎጥን፣ ብሔር እና ቋንቋን መሰረት አድጎ የሚከሰቱ ግጭቶችን በማክሸፍ እና ህብረተሰቡን የአንድነት ትስስር በማጠናከር ላይ ያተኮረ ዓላማ ያለው ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በመጨረሻም ከስልጠናው በኋላ ሰልጣኖች ከመጡበት አካባቢ ውጭ በሌሎች አካባቢዎች ለአስር ወር እንደሚመደቡ እና በተመረቁበት የሙያ መስክ ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ በስልጠናው ወቅት ያገኙት እውቀት ተጠቅመው የህብረተባችን የቀደመ የሰላም፣ አብሮነት እና የመተሳሰብ እሴትን ለመገንባት የበጎ ፈቃድ ብሔራዊ አገልግሎችን በስፋት እንደሚሰጡ ተገልጿል፡፡   

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

-------------------------------------

``ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ``

``Wisdom at the source of Blue Nile``

Thank you for visiting, inviting and sharing our Pages!

Thank you for your likes and comments too!

ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

Facebook https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube https://www.youtube.com/@bduethiopia

Instagram www.instagram.com/bduethiopia

TikTok https://www.tiktok.com/@bduethiopia

Telegram https://t.me/bduethiopia

Twitter https://twitter.com/bduethiopia

LinkedIn http://www.linkedin.com/school/bduethiopia

Website https://bdu.edu.et/

 

 

ለ20 ቀናት ሲሰጥ የቆየው የግንባታ መረጃ ሞዴሊንግ ስልጠና ተጠናቀቀ

**********************************************************

[ህዳር 13/2015 ዓ.ም፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ] በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መሬት አስተዳደር ኢንስቲትዩት Building Information Model (BIM) ቴክኖሎጂን በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ማካተትን አልሞ ለመሬት አስተዳደር ኢንስቲትዩት አርክቴክቸር ትምህርት ክፍል መምህራን፣ ለአማራ ዲዛይን ቢሮ ባለሙያዎች፣ ለፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና ባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መምህራን ለ20 ቀናት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡

በመሬት አስተዳደር ኢንስቲትዩት አርክቴክቸር ትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ ታደለ ይኸይስ ስልጠናውን አስመልክተው እንደገለጹት ስልጠናው የተጀመረው ባለፈው አመት በመሬት አስተዳደር ኢንስቲትዩት እና በኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት መካከል በጋራ ለመስራት በተስማሙት መሰረት መሆኑን ገልፀውልናል፡፡

አቶ ታደለ የስልጠናው ዋና አላማ የBIM ቴክኖሎጂን እያንዳንዱ ባለሙያ በመማር ማስተማሩ ሂደት እንዲያካትተው፣ የዩኒቨርስቲው መምህራን ቀሪ የኮንስትራክሽን ባለሙያዎችን የሚያሰለጥኑበት ማዕከላት እንዲቋቋሙ ማመቻቸት እና ከመማር ማስተማር ባሻገር የግል ቢሮ ያላቸው መምህራን በስራቸው አጋጣሚ ሁሉ የBIM ቴክኖሎጂን ተግባራዊ እንዲያደርጉ እንዲያግዝ ነው ብለዋል፡፡

ስልጠናውን የሰጡት በኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ባለሙያ አቶ ፈለቀ አሰፋ ስለስልጠናው ሲናገሩ የግንባታ መረጃ ሞዴሊንግ ወይም Building Information Model (BIM) ቴክኖሎጂን የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ከእቅድ እስከ ማፍረስ ያለውን የግንባታ ስርዓት አቀናጅቶ መስራት የሚችል ሲሆን ይህ ቴክኖሎጂ እንደ አገር በ2017 ዓ.ም አስገዳጅ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ስለዚህ ዩኒቨርሲቲዎች በካሪኩለም ያካትታሉ፣ የስልጠና ማዕከላት በማቋቋም የስልጠና ፍላጎት እንዲያሟሉ ይጠበቃል ብለዋል፡፡

አቶ ፈለቀ ስልጠናው ዲዛይን እና ግንባታው ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ፕሮጀክቶቻቸውን በBIM ቴክኖሎጂ እንዲያስገቡ እድል ይፈጥራል፡፡ ይህ ማለት ቴክኖሎጂውን ስንተገብር ኢንዱስቲሪው ላይ የሚፈጠረውን የጥራት፣ ያልተፈለገ ወጪ፣ የጊዜ ብክነት እና አለመናበብ  ችግሮችን ሁሉ መቅረፍ እንችላለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

 

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

-------------------------------------

``ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ``

``Wisdom at the source of Blue Nile``

Thank you for visiting, inviting and sharing our Pages!

Thank you for your likes and comments too!

ለተጨማሪ መረጃዎች፡-

Facebook https://www.facebook.com/bduethiopia

YouTube https://www.youtube.com/@bduethiopia

Instagram www.instagram.com/bduethiopia

TikTok https://www.tiktok.com/@bduethiopia

Telegram https://t.me/bduethiopia

Twitter https://twitter.com/bduethiopia

LinkedIn http://www.linkedin.com/school/bduethiopia

Website https://bdu.edu.et/

 

Pages