STEM አስመረቀ

                                 የSTEM ከል 2 ዙር ያሰለጥናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ማበልፀጊያ ማዕከል / Stem Incubation Center / ከባህር ዳር ከተማ ለመጡ 50 አመልካቾች በፈጠራ ስራ ላይ ያተኮረ የ6 ወር ስልጠና ሰጠ፡፡

ሰልጣኞች በማዕከሉ በነበራቸው ቆይታም  በፈጠራ ስራ ላይ ያተኮረ ውድድር አድርገው ሦስት አሸናፊዎች ወደ ቀጣዩ ውድድር ተሸጋግረዋል፡፡ አሸናፊዎች የዕውቅና የምስክር ወረቀት የተበረከተላቸው ሲሆን ፤ US Embassy, ICog Labs, JICA እና Humanity ከተባሉ ተቋማት ጋር በመሆን በኢትዮጵያ 15 ከተሞች ለሚሳተፉበት ውድድር ባህር ዳር ከተማን የሚወክሉ እንደሚሆኑም ታውቋል፡፡

በመርሃ ግብሩ የአማራ ክልል ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ሰብስበው አጥቃው የተገኙ ሲሆን አገሪቱ ለሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተለየ ትኩረት በምትሰጥበት ወቅት የማህበረሰብ ችግር ፈች የስራ ፈጠራ ስራዎች ለውድድር መቅረባቸው የተለየ እንደሚያደርገው ተናግረው ጅምሩ ይበል የሚያሰኝ ነው ብለዋል ፡፡