የጽዳት ዘመቻ

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ግቢዎች የጽዳት ዘመቻ ተካሄደ፡

በሃገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ያለውን የጽዳት ስራ ምክኒያት በማድረግ ሚያዝያ 06/2011 ዓ.ም. በዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ግቢዎች የጽዳት ዘመቻ ተካሂዷል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ መምህራን፣ ስራተኞችና ተማሪዎች የተሳተፉበት ይህ ዘመቻ ከየግቢው ቀላል የማይባል ደረቅ ቆሻሻን ከማስወገድ ባለፈ አብሮ የመስራት ባሕልን በማሳደግ ሌሎች የጋራ ርብርብ የሚፈልጉ ጉዳዩችን ሁሉ በትብብርና በጋራ በመስራት የተሻለ አካባቢን መፍጠር እንደሚቻል የታየበት ነው፡፡

ከዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች ባለፈ በዩኒቨርሲቲው ዙሪያ የሚኖሩ ወጣቶችና ሴቶችም የተሳተፉ ሲሆን በተለይም በኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጅ ኢንስቲትዩት ተሳትፎ ላደረጉት የአካባቢው ወጣቶች በተቋሙ ሃላፊዎች ምስጋናና የማስታወሻ ቲሸርት ስጦታ ተበርክቶላቸዋል፡፡ ወጣቶቹ ከዩኒቨርሲቲው ጋር ወደፊትም በዘርፈ ብዙ ጉዳዮች አብረው መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል፡፡

በተለያዩ ግቢዎች ማለትም በግብርና እና አካባቢ ሳይንስ፣ በህግና መሬት አስተዳደር፣ በዋናው ግቢ በተፈጥሮ ሳይንስ እና በሌሎችም ክፍሎች የጽዳት ዘመቻ የተካሄደ ሲሆን በዋናው ግቢ በተለይም በሳይንስ ኮሌጅ መምህራንና በጎልማሶች ትምህርት ክፍል (Adult Education) ተማሪዎችና ጥቂት መምህራን የተደረገው ግን ከሁሉም የጎላና በተምሳሌትነቱ የሚጠቀስ መሆኑን ለመታዘብ ተችሏል፡፡ ይህም የጽዳት ዘመቻ በየወሩ እንደሚካሄድ ከአስተባባሪዎቹ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡