አመታዊ አውደ ጥናት ተካሄደ

5ኛው የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የቱሪዝም ሳምንት አመታዊ አውደ ጥናት ተካሄደ
*****************************************************
የባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በቱሪዝምና ሆቴል ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል አዘጋጅነት ‹‹ የባለ ድርሻ አካላት ሚና በቅርሶቻችን እንክብካቤ ›› በሚል መሪ ቃል መጋቢት 27, 2011 ዓ.ም. የግማሽ ቀን አውደ ጥናት ተካሂዷል፡፡

በአውደ ጥናቱ በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ሳይንስ ኮሌጅ የባዮሎጂ ትምህርት ክፍል መምህር እና ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር አያሌው መለሰ በጥናታዊ ፅሁፋቸው እንዳቀረቡት ጣናን ከእንቦጭ አረም ለመታደግ መጀመሪያ የሃይቁን ድንበር ማስከበር ይገባል ሲሉ፤ ለዚህም ምክንያቱ ጣና ከላይም ከታችም እሳት እየበላው በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡ ከላይ የጣና ዳር ተራራ እየታረሰ መሆኑ፤ ከታች ደግሞ ወደ አባይና ጣና ሀይቅ የሚለቀቅ ቆሻሻ መኖሩ ምሆኑን ገልፀው ከዚህም ባሻገር ጣና በደለል በመሞላቱ ምክንያት እስከ ውሃው ዳር እየታረስ በመሆኑ 120 ኪሎ ሜትር የሚሆነው የሀይቁ አካል በድን ሆኗል ብለዋል፡፡

በአውደ ጥናቱ ከሚኒስተር መ/ቤቱ፣ ከባህር ዳር ከተማ ባህል ቱሪዝም እና ከተለያዩ ዩንቨርስቲዎች የተጋበዙ መምህራንና ባለሙያዎች ተገኝተው ውይይት አድርገዋል፡፡