ስልጠና

                         ለተማሪዎች ስልጠና ተሠጠ

በቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ እና በትምህርትና ስነ ባህሪ ኮሌጅ የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች የምርምር ስራቸውን ለማከናወን ያስችላቸው ዘንድ ስልጠና ተሰጣቸው፡፡

በኮሌጆቹ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙት የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች በመመረቂያ ፅሁፍ ዝግጅት ጊዜ ለሚያከናውኑት  መረጃን የመተንተን፣ የማደራጀት እና የማጠናከር ተግባር በብቃት ይወጡት  ዘንድ ከሚያስለፍጓቸው ክህሎት እና እውቀት ውስጥ የ statistical package for social sciences software (SPSS) ስልጠና ከሚያዚያ 07 ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት ተሰጥቷል፡፡

ስልጠናውም ከስታቲስቲክስ ትምህርት ክፍል በመጡ ሁለት መምህራን የተካሄደ ሲሆን በስልጠናው ማብቂያም በዩኒቨርስቲው የስልጠና ዳይሬክቶሬት አቶ ወርቁ አበበ እና የአጠቃላይ ጥራት አስተዳደር ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ደሳለኝ እጅጉ እጅ ስልጠናውን ላጠናቀቁ ተማሪዎች  የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡