ሰልጣኞች ተመረቁ

የትያትር ሰልጣኞች ተመረቁ

በትዕግስት ዳዊት

ሰላሣ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ባህል ማዕከል አባል ተማሪዎች  በመሉዓለም የባህል ማዕከል የትያትር አዘጋጅ በሆኑት አቶ ደሳለኝ ድረስ የሰማኒያ ሰዓት የትያትር ስልጠና ወስደው ተመረቁ፡፡

ሰልጣኞች ከትያትር ትወና በተጨማሪ የ(ሜክ አፕ) ስልጠና መውሰዳቸው የተገለጸ ሲሆን ሰልጣኞች በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ከተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ  ያሉ ሆነው የትያትር ፍቅር እና የትወና ፍላጎት ያላቸው ብቻ ተመርጠው በስልጠናው እንደተሳተፉ ተነግሯል፡፡

ስልጠናውን የሰጡት የሙሉዓለም የባህል ማዕከል የትያትር አዘጋጅ የሆኑት አቶ ደሳለኝ ድረስ የተለያዩ ድርሰቶችን በግል እና በጋራ የደረሱ ሲሆን  በተጨማሪም የቲያትር አዘጋጅ በመሆንም ስፊ ልምድ ያላቸው ናቸው፡፡ ሰልጣኞችም በሙያው እውቀትና ልምድ ባላቸው ባለሙያ በመሰልጠናቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ጭውውቶች፣ትያትሮች፣የስነ ግጥም ስራዎች እና ማይም ( ድምጽ አልባ ተውኔት ) በዩኒቨርሲቲው ባህል ማዕከል ተዋንያን ለታዳሚወች ቀርቧል፡፡

ተቋርጦ የነበረው በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ባህል ማዕከል በየሁለት ሳምንቱ ይካሄድ የነበረው የስነ-ጽሁፍ ምሽት ከያዝነው ሳምንት ጀምሮ እንደ በፊቱ እንደሚካሄድ ተገልፆ ማነኛውም ፍላጎቱ ያለው ሁሉ በፕሮግራሙ መታደም እንደሚችል ጥሪ ቀርቧል፡፡