ለአመራሩ ስልጠና ተሰጠ

ለአካዳሚክ አመራሩ በትምህርት ጥራት ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ የጥራት አስተዳደር ከከፍተኛ ትምሀርት ጥራት አግባብነት አጀንሲ (HERQA) ጋር በመተባበር ለአካዳሚክ አመራር አካላት ለአራት ቀናት የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የሚያስችል ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

የስልጠናው ዋና አዘጋጅ የአጠቃላይ ጥራት አስተዳደር ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ደሳለኝ እጅጉ መምህራን ጥራቱን የጠበቀ የመማር ማስተማር ስራ እንዲሰሩ ለማገዝ ይህ ስልጠና መዘጋጀቱን ገልፀው በስልጠና መክፈቻ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ እንዳሉት ዘመናዊ ትምህርትን ከምዕራባውያን እንደመቀበላችን ምንም እንኳን ከፍተኛ ትምህርት ከዓለም አንፃር እድሜው አነስተኛ ቢሆንም በሃገራችን ለትምህርት ጥራት የተሰጠው ትኩረት ከምዕራባውያኑ አንፃር የዘገየ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ፕሬዚደንቱ አክለውም ስልጠናው  ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አሳስበው እንደዋና ዓላማ በአመራር ላይ ያሉ የዩኒቨርሲቲው አከላት የሚያነሱትን የአመራር አቅም ግንባታ ጥያቄ ተገቢ ምላሽ እንዲያገኝ ታልሞ የተዘጋጀ እንደሆነ ገልፀው መሰል ጥያቄዎች ከዚህ በኋላ  እንደማይኖሩ እምነታቸውን ገልፀዋል፡፡ ሌላው የስልጠናው ዋና አላማ  ደግሞ  ተማሪዎችን በዓለም ደረጃ ተወዳዳሪነት ያላቸው እንዲሆኑ፣ ብሎም ችግር ለመፍታት የሚያስችል በቂ እውቀትና ክህሎት ያላቸው ሆነው እንዲመረቁ በሚደረገው ሁሉን አቀፍ ስራ አመራሩ የመሪነት ድርሻውን በአግባቡ እንዲወጣ ይችል ዘንድ ስንቅ ለመስጠት  እንደሆነ ዶ/ር ፍሬው መቁመዋል፡፡

ስልጠናው ከመጋቢት 19 እስከ 22 2011 ዓ.ም. ድረስ የሚሰጥ ይሆናል፡፡