በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሰራተኞች በመጠናቀቅ ላይ በሚገኘው የዩኒቨርሲቲው የማስተማሪያ ሪፈራል ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ውስጥ አንድነታቸውንና የስራ ውጤታማነትን ለማጠንከር የሰራተኞችን ቀን አክብረዋል፡፡በተጨማሪም ፕሮግራሙ በመሰራት ላይ ያለው ሆስፒታል ያለበትን ደረጃ ማስጎብኘትና ተጠናቆ አገልግሎት እንዲሰጥ ተሳታፊዎች የድርሻቸውን እንዲወጡ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡ በዝግጅቱ የሰባታሚት አካባቢ የአገር ሽማግሌዎች፣ከአማራ ክልል ጤና ቢሮ የመጡ እንግዶች እንዲሁም ሌሎች ተጋባዥ ሰዎች ተገኝተዋል፡፡ በፕሮግራሙ በምርምር ዘርፍ፣በህክምና አገልግሎት እንዲሁም በኮሌጁ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች እውቅና ተሰጥቷል፡፡
Bahir Dar University
Bahir Dar, Ethiopia
Phone:- +251-0582-9 99275
P.o.box:- 79
e-mail:- collegehealthscience@gmail.com
Website Design and Developed by LTTU,ICT Copyright © 2017- Bahir Dar University