የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው የመግቢያ መስፈርት መሰረት በማታ (Extension) እና በርቀት (Distance) በመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም በPGDT ተማሪዎችን ተቀብሎ ማሰልጠን ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም መስፈርቶችን የምታሟሉና መማር የምትፈልጉ አመልካቾች ከመጋቢት 7 ቀን 2014 ዓ/ም እስከ መጋቢት 21 ቀን 2014 ዓ/ም ድረስ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እያስታወቅን የምታመለክቱባቸውን የትምህርት መስኮች ዝርዝር ከዩንቨርሲቲው ሬጅስትራር ድረ ገጽ https://bdu.edu.et/registrar/ መመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡